RODAS Agency

RODAS Agency RODAS EMPLOYMENT AGENCY 0921314899

28/06/2023
13/04/2023
ማስታወቂያ  ለሚመለከተው ሁሉ  የሥራና ክህሎት ሚንስቴር ከሃገር ውስጥ እና በሃገር ውጪ ያሉ የስራ ዕድሎችን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ባለው ስራ እስካሁን ለብዙ ስራ ፈላጊዎች የስራ ...
06/04/2023

ማስታወቂያ

ለሚመለከተው ሁሉ

የሥራና ክህሎት ሚንስቴር ከሃገር ውስጥ እና በሃገር ውጪ ያሉ የስራ ዕድሎችን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ ባለው ስራ እስካሁን ለብዙ ስራ ፈላጊዎች የስራ ዕድል መፍጠር ተችሏል። በተለይም ውጭ ሃገር የስራ ስምሪት ሰፊ የሪፎርም ስራ እየተካሄደ ሲሆን በዚህም መሰረት የስራ ስምሪቱን ዲጂታላይዝ ማድረግ ተችሏል።

በመሆኑም የስምሪት መደረሻዎችን ለማስፋት ከተለያዩ ሃገራት ጋር እየገባናቸው ያሉ አዳዲስ ስምምነቶች የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሃይል ፍላጎት ያላቸው በመሆኑ በተዘረዘረው የሞያ መስክ የተጠየቀውን የትምህርት እና የስልጠና ዝግጅት የምታሟሉ እንዲሁም ተጨማሪ ስልጠና ለመውሰድ ፍቃደኛ የሆናቹ ዜጎች https://www.lmis.gov.et ድህረ-ገጽ ላይ ገብታቹ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን።

ድህረ-ገጹ ላይ በሚደረገው ምዝገባ ሲስተሙ በሚሰጠው የባዮሜትሪክስ ቁጥር ከቀናት ብኋላ የሚከናውነውን የባዮሜትሪክስ መረጃ ምዝገባ የሚጀመርበትን ቀን በወቅቱ የምናሳውቅ ይሆናል።

1. Nurse
2. Engineering
3. Architecture
4. Health care
5. Nanny
6. Cleaner
7. House Keeper
8. Baby Sitter
9. Caregiver/Caretaker
10. Security Guard/ Security Officer
11. Driver
12. Laborer
13. Cook
14. Beautician/Beauty Salon Operator
15. Specialty Arabian Food Cook

የሥራዎ ባለቤት እርስዎ ኖዎት !

Generated by create next app

 #እንድታውቁት"  #አስቸኳይ የፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው ተቋርጧል " - የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትበኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና መሥሪያ ቤት እንዲሁም በ11ዱ የክልል ቅር...
29/03/2023

#እንድታውቁት

" #አስቸኳይ የፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው ተቋርጧል " - የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

በኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና መሥሪያ ቤት እንዲሁም በ11ዱ የክልል ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች ሲሰጥ የነበረው “ አስቸኳይ ” የፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው መቋረጡን የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አሳውቋል።

አገልግሎቱ ለምን ተቋረጠ ?

አገልግሎቱ የተቋረጠው የባለ ጉዳይ ፍሰት ከመፈጠሩ ጋር ተያይዞ መጠነ ሰፊ በመስተዋላቸው ነው።

ከዚህም በተጨማሪ ተገልጋዮች ሊገለገሉ ሌሊት ላይ በሚመጡበት ወቅት በተለያዩ ህገ-ወጥ ግለሰቦች የሚደርስባቸው እንግልትና ጉዳት በአገልግሎት አሰጣጥና በተገልጋዩ ላይ ተግዳሮት በመፍጠሩ ነው።

ስለሆነም የማስተናገድ አቅም እና ሌሎች ክፍተቶች እስከሚስተካከሉ ድረስ ይሰጥ የነበረው የ “ አስቸኳይ ” ፓስፖርት አገልግሎት ለጊዜው ተቋርጧል።

አስቸኳይ ጉዞ ያላቸው በምን ይስተናገዳሉ ?

ቀድሞ ይሰራበት በነበረው አሰራር መሰረት ያላቸው አገልግሎት ጠያቂዎች ማስረጃዎቻቸውን አቅርበው ቤት ብቻ ከመጋቢት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ይስተናገዳሉ።

ማሳሰቢያ ፦ ተገልጋዮች ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ከህገወጥ ደላሎች እንዲጠነቀቁ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የመደበኛ ፓስፖርትን በተመለከተስ ?

የመደበኛ ፓስፖርት ተገልጋዮች ቀድሞ በነበረው ሂደት መስተናገድ #ይቀጥላሉ።

ምንጭ፦ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

👀
25/02/2023

👀

ያልተመዘገባችሁ ተመዝገቡ!!****የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለ4ኛ ዙር ሠልጣኞች የምዝገባ ቀናትን አራዘመ  ********************  የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢ...
25/01/2023

ያልተመዘገባችሁ ተመዝገቡ!!
****
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለ4ኛ ዙር ሠልጣኞች የምዝገባ ቀናትን አራዘመ
********************

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ለ4ኛ ዙር ላዘጋጀው ሥልጠና የሚያካሄደውን የምዝገባ ጊዜ ማራዘሙን አስተውቋል።

ለሥልጠናው ፍላጎት ያሳዩ ተመዝጋቢዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን ተከትሎ፣ በየቅርንጫፎቹ የታየው የተመዝጋቢዎች መጉላላትን ለማስቀረት፣ ተጨማሪ ተመዝጋቢዎችንም ለማካተት እና በሚፈለገው መልኩ የደንበኞቻችንን ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ፣ ምዝገባውን በእርጋታ ለማካሄድ ይቻል ዘንድ እስከ መጪው እሑድ ጥር 21 ቀን 2015 ድረስ ምዝገባው ለ4 ተከታታይ ቀናት ማራዘሙን የባንኩ ማኔጅመንት ገልጿል።

በመሆኑም ተመዝጋቢዎች በቀሪዎቹ ቀናት ተረጋግተው ምዝገባቸውን እንዲያካሂዱ ባንኩ አሳስቧል።

ይህንኑ በማስፈጸም ላይ ላሉ የባንኩ ቅርንጫፎችም መመሪያ መተላላፉ ታውቋል።

04/01/2023
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሁለታት ዓመት የሽሬ በረራ ዛሬ ዳግም ጀምሯል          >>> "ወደ ሽሬ በረራ መጀመሩ ስንፈልገው የነበረው ሰላም ማረጋገጫ ነው - መንገደኞችታኅሣሥ 24/201...
02/01/2023

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሁለታት ዓመት የሽሬ በረራ ዛሬ ዳግም ጀምሯል

>>> "ወደ ሽሬ በረራ መጀመሩ ስንፈልገው የነበረው ሰላም ማረጋገጫ ነው - መንገደኞች

ታኅሣሥ 24/2015 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሽሬ በረራ መጀመሩ ስንፈልገው የነበረው ሰላም ስለመምጣቱ ማረጋገጫ ነው ሲሉ መንገደኞች ገለፁ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሁለታት ዓመት በላይ ተቋርጦ የነበረውን የሽሬ በረራ ዛሬ ዳግም ጀምሯል።

የሽሬ መንገደኞች ለኢዜአ እንዳሉት፣ ከቤተሰቦቻቸው ጋር የነበረው ግንኙነት ከሁለት ዓመታት በላይ ተቋርጦ ነበር።

ይሁን እንጂ መንግስት በሰላም ስምምነቱ መሰረት ወደ ሽሬ የሚያደረገውን በረራ ዛሬ አስጀምሯል ብለዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሽሬ የሚያደርገው በረራ ስንፈልገው የነበረው ሰላም ስለመምጣቱ ማረጋገጫ ነው ብለዋል።

አሁን በተፈጠረው ነገር ደስ ብሎናል ያሉት መንገደኞቹ፣ ሰላም የሁሉም መሰረት በመሆኑ አሁን የሰፈነው ሰላም ዘላቂነት እንዲኖረውም ጠይቀዋል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when RODAS Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to RODAS Agency:

Share