19/01/2026
Timket is one of the primary public festivals celebrated by the Ethiopian Orthodox Church. The festival commemorates the baptism of our Lord and Savior Jesus Christ in the Jordan River by John the Baptist. The celebration is a three-day event, with a colorful religious and cultural practices.
On the eve, known as Ketera, the Tabots, which are the sacred replicas of the Ark of the Covenant, are taken out of the churches. They are escorted to a nearby river or a designated pool of water amidst great cheering and hymns. This signifies Jesus Christ’s journey to the Jordan river. The Tabots stay overnight in specially prepared tents, where the night is spent in prayer, hymns, and the Divine Liturgy.
On the day of the feast, prayers are conducted at the baptismal site starting from the morning. The blessed water is then sprinkled upon the gathered people. Following extensive performances of Wereb and spiritual songs by priests, deacons, and choirs, the Tabots are escorted back to their respective churches by the massive crowd that accompanied them. The following day marks the feast of Kana Ze Galila (the Wedding at Cana), during which the Tabot of St. Michael, which remained at the site, is escorted back to its church.
Timket is one of the main festivals for which Ethiopia is known worldwide. Six years ago, it was inscribed by UNESCO as an Intangible Cultural Heritage of Humanity.
#ጥምቀት
የጥምቀት በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በአደባባይ ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንዱና ዋናው ነው። በዓሉ ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰላሳ አመቱ በዮርዳኖስ ወንዝ በዮሐንስ መጠመቁን፣ መንፈስ ቅዱስ ከሰማይ በርሱ ላይ የመውረዱን ነገር የምታከብርበት በዓል ነው።
በዓሉ ከዋዜማው እለት ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚከበር ልዮ በዓል ነው። በበዓሉ ዋዜማ በከተራ እለት ታቦታት ከቤተክርስትያናት ወጥተው ህዝቡን እየባረኩ በአቅራቢያቸው ወዳለው ወንዝ ወይም የተገደበ ውሀ በትልቅ እልልታና ዝማሬ ታጅበው የሄዳሉ። ይህም ኢየሱስ ክርስቶስ ወድ ዮርዳኖስ መሄዱን ለማመልከት ነው። በዚያም በተዘጋጀላቸው የታቦት ማደሪያ ሆነው ሌሊቱን በዝማሬ እና በቅዳሴ ያሳልፋሉ።
በበዓሉ እለትም ከጠዋት አንስቶ በባህረ ጥምቀቱ ጸሎት ይደረጋል። የተጸለየበት ውሀም በዚያ በተሰበሰበው ምዕመን ላይ ለቡራኬ ይረጫል። ከዚያም በቀሳውስትና፣ ካህናት እና መዘምራን ወረብና ዝማሬዎች በሰፊው ከቀረቡ በኋላ ታቦታቱ ይዟቸው በመጣው ህዝብ ታጅበው ወደየአብያተክርስትያናቱ ይመለሳሉ። በማግስቱም የቃና ዘገሊላ በዓል የሚታሰብ ሲሆን፣ በማደሪያ የቀረው የቅዲስ ሚካኤል ታቦት ወደቤተክርስትያኑ ይሸኛል።
የጥምቀት በዓል ኢትዮጵያ በመላው አለም ከምትታወቅባቸው በዓላት ዋነኛው ሲሆን ከስድስት አመታት በፊት በአለም አቀፉ የትምህርት፣ የባህልና፣ የሳይንስ ተቋም ዮኔስኮ አማካኝነት በማይዳሰሱ ቅርሶች ስር ተመዝግቧል።
Melkam Timket🍋💛
#ጥምቀት #ከተራ #ኦርቶዶክስ #ኢትዮጵያ #ምድረቀደምት #ቼበለው
Subscribe to our social media
Telegram: https://t.me/chebelewethiopia
Instagram: https://www.instagram.com/che_belew_ethiopia?igsh=MTB5NG5zMTlvbzU0Zw==
Facebook: https://www.facebook.com/share/1AqUz5QmZj/?mibextid=qi2Omg