04/11/2025
ከቦታው
ምሽት 3 ሰዓት። ከአውላ የጉዞ ወኪል ጋር በመተባበር በመጀመሪያው ዙር የዑምራ ጉዞ ከተሳተፍን ጥቂት ተጓዦች ጋር፣ ከመስጂደል ሐራም በሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ የኮንትራት ታክሲ ይዘን ወጣን። በግምት አምስት ኪሎ ሜትር ያህል ከተጓዝን በኋላ፣ በግርማ ሞገስ ወደቆመው ጀበለ ኑር (የብርሃን ተራራ) ግርጌ ደረስን። ይህ ሰማይ ጠቀስ ተራራ ከባሕር ወለል በላይ 642 ሜትር ገደማ ከፍታ እንዳለው የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ይጠቁማሉ።
በዚህ ተራራ አናት ላይ የሚገኝ አንድ ታሪካዊ ጎድጓዳ ስፍራ አለ። የሒራእ ዋሻ ይሰኛል። ከስሩ ሽቅብ ወደ ተራራው ጫፍ ሲመለከቱ፣ አቀበቱ ወደ ሰማይ የሚወጣ ግዙፍ መሰላል የመሰለ አስፈሪ ገጽታ መላበሱን ያስተውላሉ። ይህን ፈታኝ አቀበት ከሦስት ዓመታት በፊት የመውጣት ዕድል አጋጥሞኝ ነበር። በወቅቱ፣ ተራራውን ከእግር እስከ አናቱ ለመጨረስ የፈጀብኝ 38 ደቂቃዎች ብቻ ነበር።
ዘንድሮ ደግሞ፣ በምሽቱ የመካ ነፋሻማ አየር ታግዘን፣ በጋራ በጀመዓ አቀበቱን መውጣት ጀመርን። በመንገዳችን ላይ በተደጋጋሚ የምናገኛቸው የደቡብ፣ የደቡብ-ምሥራቅ እና የመካከለኛው ኤዥያ አገራት ዜጎች ናቸው። ጀርባቸው ላይ መቀነት አስረው መሬቱን ላፍ ላፍ እያሉ የሚወጡ የቱርክ አረጋውያንንም አስተውለናል። በተለይም ከደቡብ ኤዥያ የመጡት ዜጎች፣ ተራራውን በተደጋጋሚ የመውጣት ልምድ ያካበቱ ይመስል፣ እንደ አትሌት በቅልጥፍና ሲያልፉን ነበር።
የእኛ ጉዞ ቀስ ያለ ነበር፤ እንዲያውም ከኤሊ ትንሽ የፈጠነ እንጂ የሚያስደንቅ ፍጥነት አልነበረንም። የጋራው ጉዞ በደካማው ተጓዥ ፍጥነት መጓዝ ስለነበረበት፣ የተወሰነ ወደ ኋላ ቀርተናል። የልባችን ምት ካኒቴራችንን ማራገብ ሲጀምር ልብ ስራዋን ለማቆም የዳዳት ይመስላል። አልፎ አልፎ መንገድ ላይ ውሃ የሚሸጡ ሰዎች ባይኖሩ ኖሮ፣ ምላሳችን ከላንቃችን ተጣብቆ ድምጻችን ይሰወር ነበር።
እንደምንም ብለን፣ ከ55 ደቂቃዎች ፈታኝ ጉዞ በኋላ፣ የተራራው ጫፍ ላይ ደረስን። በብርሃን ያሸበረቀችውን መካ ቁልቁል ስንመለከት፣ ከ14 ክፍለዘመናት በፊት ጭል ጭል በሚል የቀንዲል ብርሃን የምትታወቀው መካ፣ በዓይነ-ሕሊናችን ታየችን። በኡስታዝ ዐብዱረሕማን ሙሐመድ የሚመራው የምሽት ቅፍለትም ቁርኣን ለመጀመሪያ ጊዜ በወረደበት የተራራው ክፍል ሰፈረ። ጋሩ ሒራእ እያለም በቦታው እንዲህ ዘመረ።
«ጉዞዎ በአደራችን»
አውላ የጉዞ ወኪል፣ ቀጣይ ከታህሳስ 11 ቀን 2018 ዓ.ል እስከ ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓ.ል ለሚያደርገው ሁለተኛ ዙር የዑምራ ጉዞ፣ እንግዳ ሆናችሁ ከኛ ጋር ያማረና ምቹ ቆይታ እንድታደርጉ በሩን ከፍቶ ይጠብቃችኋል።