19/05/2026
ሰሞኑን በሚዲያችን ውስጥ የፖለቲካ ክርክርና ቅስቀሳ በአማሮ ወይም በኮሬተ ቋንቋ “ኮርሶ” አካባቢ መጠላለፍ የበዛበት ስልት እያየን ነው። ቤተሰብ፣ ይህ ምርጫ ካለፈ በኋላ አብረን እንደምንኖር ስለምናውቅ ዛሬ ማንንም ለመተቸት አልመጣንም። ዋናው ተልዕኳችንም ያ አይደለም። ነገር ግን በማኅበራዊ አኗኗራችን ላይ ክፉ ዘር እየተዘራ ስለሆነ ምርጫው ካለፈ በኋላ ሁላችሁንም በደንብ እንወቅሳችኋለን።
እና !
ትችት በጉዳዩ ውስጥ እያነሳችሁ የምትጠቀሙትን የቃላት አጠቃቀም በተመለከተ ነው። ምክንያቱም ቃላት ኮሬተን፣ ኮሬተ ደግሞ ኮሩንተን የገነቡበት አውድ የራሳቸው መሠረታዊ ትርጉምና አጠቃቀም አላቸው።
በKWT እምነት፣ በዚህ የፖለቲካ ትኩሳት ውስጥ ያነሳችሁት ጉዳይ የቃላት አጠቃቀም ብቻ ሳይሆን ቃላቶች በኮሬ ባህል ውስጥ ያላቸው የሥልጣን ትርጓሜ፣ የታሪክ አውድ፣ የፖለቲካ አመለካከት እና የሕዝብ ግንዛቤ ጉዳይ ስለሆነ ትክክለኛ የውይይት ነጥብ አድርገን ለዛሬ መርጠናል።
“የኮሬ ባህላዊ ንጉሥ” የሚለው አገላለጽ በአካዳሚክ ወይም በመንግሥታዊ ጽሑፎች ውስጥ አንዳንድ ጊዜ የንጉሡን ሚና “cultural” ብቻ አድርጎ ለመግለጽ ስለሚጠቀም የሥልጣኑን ታሪካዊና ማኅበራዊ ስፋት ሊያሳንስ ይችላል። በተለይ በኮሬ ሕዝብ ውስጥ “ካቴ” የሚለው ማዕረግ በቀላሉ ceremonial ወይም symbolic ብቻ ተብሎ የሚታይ አይደለም። ታሪካዊ፣ ማኅበራዊ፣ ዳኝነታዊ፣ የእርቅና የማንነት ውክልና ሚናዎችን የያዘ ተቋም መሆኑን ሁላችንም ማወቅ አለብን።
ስለዚህ “የኮሬ ካቴ” ብሎ መጥራት በባህሉ ውስጥ ያለውን ሙሉ አውድ ይጠብቃል የሚለው አመለካከታችን ጠንካራ መሠረት አለው። ምክንያቱም “ባህላዊ ንጉሥ” የሚለው ቃል በዘመናዊ ፖለቲካ አውድ ውስጥ “ፖለቲካዊ ሥልጣን የሌለው” የሚል ንዑስ መልዕክት ሊያስተላልፍ ይችላል።
በሌላ በኩል “traditional king” ወይም “cultural king” የሚሉ ቃላት በአፍሪካ ብዙ ሀገራት የሕግና የአካዳሚክ ጽሑፎች ውስጥ የሚጠቀሙ ቢሆንም እነሱን የሚጠቀሙ ሰዎች ሁሉ የካቴውን ሥልጣን ለማሳነስ ነው ማለት አይደለም። ሆኖም በዚህ የፖለቲካ ትኩሳት ወቅት ለምን እየተደጋገመ ጥቅም ላይ እየዋለ እንደመጣ መመልከት ተገቢ ነው። ስለዚህ ቃሉ በሕዝቡ ውስጥ የሚፈጥረው ግንዛቤ ትልቅ ጥንቃቄ ይፈልጋል።
ስለዚህ እንደ አስተያየታችን፦
• “የኮሬ ካቴ”
• “የኮሬ ንጉሥ”
• “ካቴ አዳማ አሶማ” ወይም ለዞናዊ መድረክ
• “ካቲ አሶማ አዳማ”
የሚሉ አጠራሮች ታሪካዊና ባህላዊ አውዱን በተሟላ መልኩ ሊወክሉ ስለሚችሉ በዘፈቀደ መጠቀም ያልተገባ ተገማችነትና ትችት ውስጥ ሊመልሰን ይችላል።
መረዳት የሚገባችሁ ነገር ደግሞ በቃላቱ በኩል ማስተላለፍ የፈለግነው መልዕክት “ስለ ኮሬ ካቴ ምን ዓይነት የሥልጣን ግንዛቤ ለማኅበረሰቡ እየተሰጠ ነው?” የሚል መሆኑ ነው። ይህም ተገቢ የሕዝብ ውይይት የሚፈልግ ጉዳይ ነው።
ስለዚህ የጋራ ፖለቲካዊ ይዘቱን እስካልዝን ድረስ “የኮሬ ባህላዊ ንጉሥ” ከማለት ይልቅ “የኮሬ ካቴ”፣ “ንጉሳችን” ወይም “የኮሬ ንጉሥ” የሚለውን ብቻ ብታዘወትሩ የተሻለ ይሆናል።
#ታረሙ
ግንቦት 10/2018
አማሮ/ኮርሶ፣ ኬለ፣ኢትዮጵያ