26/06/2023
በ1313 ዓ.ም. በአቡነ ዘዮሐንስ የተመሠረተው
ገዳም። አቡነ ዘዮሐንስ "ከሰባቱ ከዋክብት" ደቀ መዛሙርት አንዱ ናቸው። በሁለት መንትያ ደሴቶች ላይ የወንዶችን ክብራን ገብርኤል እና የሴቶችን እንጦስ ኢየሱስ ገዳምን የመሠረቱት ናቸው። ገዳሙ በጣና ሐይቅ ደቡባዊ ክፍል ባለች ደሴት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ከባህርዳር ከተማ 8 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ በጀልባ 20 ደቂቃ ይወስዳል።
በዚህ ገዳም የንግሥት ዘውዲቱ አልባሳት፣ የንጉሥ አዲያም ሠገድ እያሡ የወርቅ መመዘኛ የብረት ሚዛን፣ የ260 ፍየሎች ቆዳ የጨረሰ እና 17 ኪሎ ግራም የሚመዝን ብራና መጽሐፍ፣ የጎጃም ንጉሥ ተክለሃይማኖት ተደራራቢ አልጋ ከነምንጣፉ እና ሌሎችም ውድ ቅርሶች የሚገኙበት ገዳም ነው።