20/02/2026
ሆስፒታሉን ዘግቶ የተፈጥሮ ሀብቱን መዛቅ አይቻልም‼️
በዎላይታ ዞን በኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ ከፍተኛ የሆነ የከሰል ክምችት መኖሩን የማዕድን ሚኒስቴር ማሳወቁን ተከትሎ በኦቶና ሆስፒታል ጉዳይ የተቀጣጠለውን ተቃውሞ ለማርገብ እየተጠቀሙበት ይገኛሉ። በመሠረቱ ከአከባቢው ታማኝ ምንጮች እንዳረጋገጥነው ከአመታት በፊት ጀምሮ መንገድ እንኳን ሳያወጡ በዝምታ ዎላይታን እየመጠጡ ያሉ እንጂ አዲስ እንዳልሆነ ሰምተን አዝነናል።
የማዕድን ክምችት ያለበት ኪንዶ ዲዳዬ መንገድ የለውም መንገድ ሳይሰሩ ሀብቱን የሚዝቁ ጨካኞች ለምን ፋብሪካ በአከባቢው አይሰሩም? ዳውሮ ዞን እና ቦሮዳ ወረዳ የከሰል ድንጋይ ማጠብያ ፋብሪካ ተገንብቷል እንዲሁም እያንዳንዱ መኪና ለአከባቢው መንግስት 20,000 ብር ገቢ አስገብቶ ነው ከሰሉን የሚጭኑት ዎላይታ ግን ስንት ስራ አጥ ይዞ በዝምታ ሀብቱን ይመዘበራል???
ፋብሪካ እገነባለሁ ያለውን ባለሀብታችንን የጋሞ ፅንፈኞች በእስር እያሰቃዩት መንገድ ፋብሪካ የሌለው የኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ ሕዝብ ችግሩ ሳይቀረፍ ሀብቱን መጠበቅ አለበት የዞኑ መንግስት ይህን ጉዳይ እንደተራ ማየት የለበትም A nation that can't control its energy sources can't control its future (የሀይል ምንጩን የማይቆጣጠር ሕዝብ ነገውን ሊቆጣጠር አይችልም) ባራክ ኦባማ እንዳሉት‼️
አንዘነጋም ኦቶና ቀይ መስመራችን ነው‼️