ኮረማሽ-Koremash

ኮረማሽ-Koremash የኢትዮጵያን ታሪክ ወግና ባህል ውብ በሆነ መልክ ይዳሰሳል ። አብረውን በመጓዝ የኢትዮጵያ ሰው ሰራሽና ተፈጥራዊ ቦታዎች ይጎብኙ። ኮረማሽ የጉዞ ማህበር !

ግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ.ም ከ 35 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የቀድሞ የኢሕድሪ/ ፕሬዝዳንት የኢትዮጵያ ህዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑሊክ/ የኢሠፓ  (የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ) ዋና ፀሀፊ...
21/05/2026

ግንቦት 13 ቀን 1983 ዓ.ም

ከ 35 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የቀድሞ የኢሕድሪ/ ፕሬዝዳንት የኢትዮጵያ ህዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑሊክ/ የኢሠፓ (የኢትዮጵያ ሠራተኞች ፓርቲ) ዋና ፀሀፊ የነበሩት ጓድ መንግስቱ ሃይለማርያም (ሌ/ኮ) ከአገር ወጥተው ወደ ሀገረ ዙምባቡዌ የሄዱበት ዕለት ነው።

ግንቦት 10 ቀን 1983 ዓ.ም ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማሪያም በመኖራያ ቤታቸው ለከፍተኛ ባለስልጣኖቻቸው የእራት ግብዣ አደረጉ ፤ ግብዣው ሲጠናቀቅ ፕሬዘዳንቱ ከዚህ በፊት ባልተለመደ መልኩ ሁሉንም ተጋባዥ እንግዶች እበራፋቸው ላይ በመሆን አንድ ባንድ እየጨበጡ ሸኙዋቸው።

ግንቦት 12 ቀን 1983 ዓ.ም ፤ ፕሬዘዳንት መንግስቱ መሉውን ቀን የተለያዮ ወረቀቶችን እቢሯቸው ውስጥ ሲቀዳድዱ ዋሉ ፤ ማምሻው ላይ ግን ወደ ዘመቻ መምሪያ በማምራት ለከፍተኛ የጦር አዛዦቻውቸው ንግግር አደረጉ።

ማክሰኛ ግንቦት 13 የፕሬዘዳንቱ ልዮ ረዳት ሻምበል መንግስቱ ፤ብላቴ ማሰልጠኛ ጣቢያ ደርሶ ከዚያም ወደ አስመራ ደርሶ መልስ የሚበቃ ነዳጅ የሞላ አንድ ዳሽ 5 አውሮፓላን እንዲዘጋጅ ትእዛዝ አስተላለፋ።

በዛው እለት ከጠዋቱ ወደ 2 ሰአት ገደማ ፕሬዘዳንቱ ከተመረጡ አጃቢዋች እንደዚሁም ከሶስተኛ ክፍለጦር የመጣና የቅርብ አጃቢያቸው ከነበረው ከሻንበል ደመቀ ባንጃው ጋር በመሆን በኮ/ል ተስፋዬ መሪነት ቦሌ አውሮፓላን ማረፊያ በመድረስ ተዘጋጅታ ትጠብቅ ከነበረችው አውሮፓላን ተሳፈሩ።

©️ አብዮቱና ትዝታዬ (ሌ/ኮሎኔል ፍሥሐ ደስታ)

ጓድ ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማርያም ለ የመጀመሪያዎቹ ወደ ኩባ ለትምህርት የተላኩ አዳጊ ወጣቶች አሸኛኘት እያደረጉ ነው። ቦታው ታጠቅ ጦር ሰፈር የነበረ ሲሆን ሊቀመንበሩ በቀኝ እጃቸው ያቀ...
18/05/2026

ጓድ ሊቀመንበር መንግሥቱ ኃይለማርያም ለ የመጀመሪያዎቹ ወደ ኩባ ለትምህርት የተላኩ አዳጊ ወጣቶች አሸኛኘት እያደረጉ ነው። ቦታው ታጠቅ ጦር ሰፈር የነበረ ሲሆን ሊቀመንበሩ በቀኝ እጃቸው ያቀፏትን ህጻን ጎንበስ ብለው በአባታዊ ፍቅር እየተመለከቷት ነው። ጓድ ሊቀመንበሩ ፊታቸውም ላይ ፈገግታ ይነበባል።

ፎቶግራፉ በ1969/70 ዓም የተነሳ ሲሆን ፎቶ አንሺዋ ብሪጊታ ቤንሲንግ ትባላለች።
(Photographer: Brigitta Benzing)

የአዲስ አበባ ራስ ሆቴል ተመርቆ የተከፈተ ቀን የተነሳ ፎቶግራፍ ነው። በ1940 ዓም ነበር ይመስለኛል።ከግራ ወደ ቀኝ፦ ጄኔራል ተድላ መኮንን፣ ኮሎኔል መንግስቱ ነዋይ እና ማንነቱ ያልታወቀ ...
18/05/2026

የአዲስ አበባ ራስ ሆቴል ተመርቆ የተከፈተ ቀን የተነሳ ፎቶግራፍ ነው። በ1940 ዓም ነበር ይመስለኛል።

ከግራ ወደ ቀኝ፦ ጄኔራል ተድላ መኮንን፣ ኮሎኔል መንግስቱ ነዋይ እና ማንነቱ ያልታወቀ አሜሪካዊ።

የውልደታቸው ቀን እና የህልፈታቸው ቀን ተመሳሳይ የሆነው የሙዚቃ ሊቁ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ (ግንቦት 8)የተወለዱት ግንቦት 8 ቀን 1930 ዓ.ም ህይወታቸውም ያለፈው በተመሳሳይ ዕለት ግንቦ...
17/05/2026

የውልደታቸው ቀን እና የህልፈታቸው ቀን ተመሳሳይ የሆነው
የሙዚቃ ሊቁ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ (ግንቦት 8)

የተወለዱት ግንቦት 8 ቀን 1930 ዓ.ም ህይወታቸውም ያለፈው በተመሳሳይ ዕለት ግንቦት 8 ቀን 1990 ዓ.ም (በ 60 ዓመት ዕድሜያቸው ፤

"የሙዚቃ ሊቁ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ"

ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ ግንቦት 8 ቀን 1930 ዓ.ም ተወለዱ። ከአባታቸው ግራዝማች ከበደ አድነው ሲሆኑ ከልጅነታቸው ጀምሮ የሙዚቃ ስሜትና ፍቅር ያሳደሩባቸው እናታቸው ወ/ሮ ፋንታዬ ነከሬ ነበሩ። አያታቸው ሊቀመኳስ አድነው ጎሹ ደግሞ የአድዋ አርበኛ እና የንግስት ዘውዲቱም ታማኝ አማካሪ እንደነበሩ ይነገራል። የሙዚቃ ፍቅር ገና በልጅነታቸው ያሳዱሩባቸው እናታቸው ገና የዘጠኝ ዓመት ልጅ ሳሉ ነበር በሞት የተነጠቁት።

መሠረታዊ ትምህታቸውን በዳግማዊ ምኒሊክ ት/ቤት እና በቀ.ኃ.ሥ 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት(ኮከብ ጽባሕ) ካጠናቀቁ በኃላ በሐረር የመምህራን ማሠልጠኛ ኮሌጅ ተመርቀዋል። ከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኒው ዮርክ ክፍለሃገር ከሚገኘው የሮቼስተር ዩኒቨርስቲ "ኢስትማን የሙዚቃ ትምህርት ቤት 1954 ዓ.ም በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁ በኃላ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰው የያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት መሠረቱ የዚሁ ትምህርት ቤትም የመጀመሪያው ዳይሬክተር ከመሆናቸውም ባሻገር በአዲስ አበባ የወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማህበር (ወ.ወ.ክ.ማ) በቀ.ኃ.ሥ የበጎ አድራጎት ድርጅት መርሓ - ዕውራን ት/ቤት እና በመሳሰሉ የወጣቶች ማህበራት እየተገኙ የሙዚቃ ትምሀርት ይሰጡ ነበር።

የያሬድ ት/ቤት ዳይሬክተር ሆነው ከ 1955 እስከ 1958 ዓ.ም ድረስ ባገለገሉበት ወቅት በንጉሰ ነገስቱ "ብሔራዊ የሙዚቃ አቀናባሪ" ተብለው ከመሠየማቸው ሌላ ለባህላዊ ጉዳዮች ላደረጉት የላቀ ተዋፅዖ በ 1954 ዓ.ም የቀ.ኃ.ሥ በጎ አድራጎት ድርጅት ተሸላሚ ሆነዋል የቀ.ኃ.ሥ የ75ተኛ የልደት በዓል በተከበረበት በዚሁ ዓ.ም በሀንጋሪ መንግስት ተጋብዘው ወደ ቡዳፔስት በመጓዝ ታዋቂውን

> እና > የተባሉትን ሁለት ድርስቶቻቸውን በአቀናባሪነት በኦርኬስትራ መሪነት አቅርበዋል ፣ በሸክላ አሳትመዋል። ገቢውም በወቅቱ በቀ.ኃ.ሥ የበጎ አድራጎት ድርጅት ስር ይተዳደር ለነበረው የመርሓ ዕውራን ት/ቤት ለግሰዋል።

ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ ጥቁር ኮዳሊ የሚለውን ማቆላመጫም ያገኙት የረቀቁ ሙዚቃ ድርሰታቸውን በሀንጋሪያ ውስጥ "ካፊልሃርሞኒክ ኦርኬስትራ ጋር በሳቸው ሙዚቃ መሪነት ባቀረቡት ጊዜ ነበር።

የኢትዮጵያ ቴሌቭዢን ለተመልካቾች ባቀረበው የህይወት ታሪክ ዳሰሳ ቅንብር ላይ አብሮ አደግ ጓደኛና ሚዜያቸው የነበሩት ደራሲ አቶ አስፋው ዳምጤ ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ ከያሬድ ት/ቤት መልቀቅና ወድያውኑ ከአገራቸው ለመሠደድ ያበቃቸው ጉዳይ ላይ አስተያየታቸውን ሲሰጡ:-

የተማሪዎች የረቂቅ ሙዚቃ ቅንብር በአ/አ ማዘጋጃ ቤት አዳራሽ አዘጋጅተው ንጉሠ ነገስቱ እንዲገኙ በሚኒስቴሩ በኩል ያቀረቡት ጥሪ እንደሚደርስ ባለመተማመን በሌላ መንገድ አድርሰው ንጉሡ ነገስቱ በተገኙበት ለህዝብ ቀርቦዋል። ሆኖም በዚሁ የተቀየሙት ሚኒስትሮችና የቀጥታ አለቆቻቸው በያዙት ቂም እሳቸውን ከዳሬክተርነት አውርደው በምትካቸው አንድ ግለሰብ የክቡር ዘበኛ ባንድ ተጫዋች የነበረው የውጭ ዜጋ አስገቡ።

"አገር ትቶ ሲሄዱ አይ ፣ እኔ መቼም በገዛ ሀገሬ ሁለተኛ ዜጋ አልሆንም ፣ ብሎኛል ይላሉ።

ፕሮፌሰሩ በስደት ዘመናቸው ለከፍተኛ ትምህርት ወደ አሜሪካ በተመለሱ ወቅት የሙዚቃ ጥናታቸው አጠናቀው ፣ የማስትሬት ዲግሪ በ 1981 ዓ.ም ፣ በዶክትሬት ዲግሪ ደግሞ በ 1983 ዓ.ም ከዌስሊያን ዩኒቨርስቲ ተመረቁ። ከ 1982 እስከ 1988 ዓ.ም ድረስ በኒውዮርክ ዩኒቨርስቲ "ክዊንስ ኮሌጅ እና በማሳቹሴትስ ብራንዲስ ዩኒቨርስቲ በረዳት ፕሮፌሰርነት ሲያገለግሉ ከቆዩ በኃላ ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ድርስ ለ 19 ዓመታት በፍሎሪዳ ዩኒቨርስቲ መጀመሪያ በፕሮፌሰርነትና በኃላም የዩኒቨርስቲው "የጥቁር አሜሪካውያን የባህር ማዕከል" ዳሬክቶር በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

በተጨማሪ የዶክተር መላኩ በያን የአዕምሮ ጥንስስ የነበረውን "የኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥናትና ምርምር ድርጅት" ዳሬክተር በመሆን አገልግለዋል።

ፕሮፌሰር አሸናፊ ከመጀመሪያ ሚስታቸው ወ/ሮ ዕሌኒ ገብረመስቀል ጋር ያፈሯቸው ኒና እና ሰናይት የተባሉ የ2 ሴት ልጆች አባት ሲሆኑ ሰናይት አሸናፊ በአሜሪካ የታወቀች ተዋናይት ናት። 3ተኛ ልጃቸው ያሬድ አሸናፊ ደግሞ ከአሜሪካዊቷ ሁለተኛ ሚስታቸው የተወለደው ነው።

ፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ በ 60ኛው የልደት በዓላቸው ዕለት በመኖሪያ ቤታቸው ግልፅ ባልሆነ ምክንያት ሞተው የተገኙ ሲሆን ፣ ምናልባት የራሳቸውን ህይወት ሳያጠፉ እንዳልቀሩ ብዙዎች ይገምታሉ።

አቶ አበራ ሞልቶት የተባሉ ወዳጃቸው ለኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በሰጡት ቃል ምልልስ ላይ ከዕለተ ሞታቸው በፊት ጽፈውላቸው እንደነበረና ደብዳቤውም በመጥቀስ > እንደሚል አስረድተዋል።

ዘመዳቸው አቶ በቀለ አሳምነው ደግሞ በዚሁ ቴሌቭዥን ጣቢያ ላይ ስለዚህ ጉዳዩ ሲያብራሩ።

ታንክ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለመምጣቱ    ታንክ የሚባል የጦር መሳሪያ ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ የታየው በ1920  ዓም ነበር።     ይሄውም የኢጣልያ መስፍን ዱክ ዴል አብሩዚ ባለፈው አመት ለጉብኝት...
17/05/2026

ታንክ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለመምጣቱ

ታንክ የሚባል የጦር መሳሪያ ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ የታየው በ1920 ዓም ነበር።

ይሄውም የኢጣልያ መስፍን ዱክ ዴል አብሩዚ ባለፈው አመት ለጉብኝት መጥተው ሳሉ ለልኡል አልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮነን ስለ ወዳጅነት የሰጧቸው ገፀ በረከት ነው።
ታንኩን ነድቶ ያመጣው ኢጣልያዊ ሙሴ ዲማርቲኒ በደመዎዝ ተቀጥሮ በልዑል አልጋ ወራሽ ግቢ የጦር መሳሪያ ግምጃ ቤት ሹም በሆነው በግራዝማች ወልደዩሐንስ ወልደ አብ ሰራተኛ ሆኖ የታንኩን አነዳድ ለተመረጡ የግቢ አሽከሮች ያስተምር ጀመር።
እነርሱም
1 ገብረ መድህን ጎሳ
2 በቀለ ሃይሌ
3 አሰፋ ወልደ ገብርኤል
4 ለማ ወልደ ገብርኤል
5 ውድነህ አበበ
6 ብዙአየሁ ወልደ ዩሐንስ የተባሉ እና ሌሎችም ናቸው።

እነዚህ አሽከሮች በቶሎ ተምረው በቅርብ ጊዜ ውስጥ ታንክ ሲነዱ ስለታዩ ተመሰገኑ።
ዲማርቲኒ የወር ደመወዙ 325 ብር እነንደነበር እና በስራው ላይ ለ ሰባት አመት እንደቆየ የክፍሉ ዃላፊ ባላምባራስ ገብረወልድ አስረድተውኛል።

ዱክ ዴል አብሩዚ በስጦታ ያቀረቡት ታንክ ሁለት ሲሆን ልዑል አልጋ ወራሽም በዚያው አይነት ሌሎች አምስት ታንኮች ከአውሮጳ እያስገቡ ስላስመጡ የታንኮቹ ቁጥር ሰባት ደርሰው ነበር

የሐያኛው ክፍለ ዘመን መባቻ

የአብዮታዊው ሰራዊት ጥቁር ቀን ዝክረ ግንቦት 8 1981 ዓ.ም ያልተሳካና ደም አፋሳሽ የነበረው መፈንቅለ መንግስት ሙከራልክ በዛሬዋ ቀን ከ34 ዓመት በፊት ግንቦት 8 1981 ዓ.ም በከፍተኛ...
16/05/2026

የአብዮታዊው ሰራዊት ጥቁር ቀን

ዝክረ ግንቦት 8 1981 ዓ.ም ያልተሳካና ደም አፋሳሽ የነበረው መፈንቅለ መንግስት ሙከራ

ልክ በዛሬዋ ቀን ከ34 ዓመት በፊት ግንቦት 8 1981 ዓ.ም በከፍተኛ ጀነራል መኮንኖች በፕሬዚደንት ኮሎኔል መንግስቱ ሀይለማርያም ላይ በአዲስ አበባና በአስመራ ላይ ደም አፋሳሽ ሆኖ የተጠናቀቀው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ የተደረገበት ዕለት ነው ።

ይህች ቀን በተለይም በአዲስ አበባ እና በአስመራ የመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች እቅዳቸውን ለማስፈፀም የኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያምን ለጉብኝት ከሀገር መውጣት ተከትሎ እንቅስቃሴ የጀመሩበት እለት ነበረች ።
የመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች በግንቦት 8 ቀን ረፋድ ላይ አዲስ አበባ አምባሳደር ቲያትር አካባቢ በሚገኘው የመከላከያ ሚኒስቴር ህንፃ ውስጥ በኢታማጆር ሹሙ ሜጀር ጀነራል መርዕድ ንጉሴ መሪነት የዕቅዱ አተገባበር ላይ ውይይት ይዘዋል ።

ሌ/ኮ መንግስቱ ሃይለማርያም ወደ ምስራቅ ጀርመን / GDR ለጉብኝት ለመጓዝ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ውስጥ ገብተዋል ። የመፈንቅለ መንግስቱ መሪዎች የኮ/ል መንግስቱን አገዛዝ ለማስወገድ መከላከያ ሚኒስቴር ህንፃ ውስጥ የዕቅድ አፈፃፀም ውይይት ላይ ነበሩ ።

ጀነራሎቹ "ኮሎኔሉን በአየር ላይ እንዳሉ በአየር ኃይል ጀቶች ይመቱ አሊያም በአየር ኃይል ጀቶች ተገደው አስመራ አርፈው በቁጥጥር ስር ይዋሉ " በሚለው ቁልፍ የመፈንቅለ መንግስቱ ጉዳይ ላይ መስማማት ላይ ሳይደርሱ ፕሬዚደንቱን የያዘቸው አውሮፕላን የኢትዮጵያን የአየር ክልል ለቃ ወጣች ።

አዲስ አበባ ያሉት የጦር መሪዎች እርምጃ ሳይጀምሩ ቀደም ብሎ በታሰበው የአፈፃፀም እቅድ መሰረት አስመራ የነበረው በሁለተኛው አብዮታዊ ሰራዊት ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ደምሴ ቡልቶ የተመራው ኃይል ከአዲስ አበባ በተላከለት መልእክት መሠረት አድርጎ ኮ/ል መንግስቱ እንደተወገዱ ስለተነገረው እሱ መረጃ ይዞ ወደ ማስፈፀሙ ገብቶ መንግስቱ ኃይለማርያም ከስልጣን መውረዱን በአስመራ ራዲዮ አስነገረ ።

አዲስ አበባ ያለውንም እንቅስቃሴ ለመርዳት እና ቁልፍ የተባሉ መንግስታዊ ተቋማትን የራዲዮና ቴሌቭዥን ጣቢያ ፣ አየር ማረፊያ ፣ ቴሌኮሚኒኬሽን፣ የጦር ክፍሎች ፣... ለመቆጣጠር እንዲቻል መቺ ኃይል የሆነውን ኤርትራ የነበረውን 102ኛ አየር ወለዱን በሁአሠ ም/አዛዥ በነበሩት ሜ/ጀ ቁምላቸው ደጀኔ መሪነት ከአስመራ ወደ አዲስ አበባ ላከ ።

ይሁን እንጂ በኋላ የነገሩን መበላሸት አይቶ የሀይል አሰላለፉን አስተካከለ በተባለለው የደህንነት ሚንስትሩ ኮሎኔል ተስፋዬ ወልደስላሴና በሻንበል መንግስቱ ገመቹ በሚመራው የልዩ ጥበቃ ብርጌድ አማካኝነት የአዲስ አበባው መፈንቅለ መንግስት ሙከራው አመሻሽ ላይ ከሸፈ ። ኮሎኔል መንግስቱም ከምስራቅ ጀርመን ወደ አዲስ አበባ በፍጥነት ተመለሱ ።

የአዲስ አበባው መፈንቅለ መንግስቱ በተለያዩ ምክንያቶች ከጥቂት ሰአታት በኃላ ሲከሽፍ ኢታማጆር ሹሙ ሜ/ጀ መርዕድ ንጉሴ እና የአየር ኃይል አዛዡ ሜ/ጀ አመኃ ደስታ መከላከያ ሚኒስቴር የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ራሳቸውን በታጠቁት መሣሪያ አጠፉ ። የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የነበሩት ሜጀር ጄኔራል ፋንታ በላይ ከሙከራው በኋላ ተሰውረው በፀጥታ ሃይሎች ሲፈለጉ ቆይተው ከሙከራው አራት ቀን በኋላ መከላከያ ሚኒስቴር ግቢ ውስጥ ተሸሽገው ተገኙ ። ጄኔራል ፋንታ ከተያዙ ከቀናት በኋላ እዚያው የታሰሩበት ማዕከላዊ ምርመራ ግቢ ውስጥ ባልታወቀ ምክንያት ተገደሉ ።

ሌላው የመፈንቅለ መንግስቱ ዋና ጠንሳሽ የዘመቻ መምርያ ኃላፊ የነበሩት ሜ/ጀነራል አበራ አበበ ጠንሳሾቹን ለማነጋገር የመጡትን የወቅቱን የመከላከያ ሚኒስቴር የነበሩትን ሜ/ጀነራል ኃ/ጊዮርጊስ ሀ/ማርያምን በሽጉጥ ክፋኛ አቁስለው ከጊቢው በአጥር ተንጠላጥለው አመለጡ ።

1/ ሜ/ጀ ኃይሉ ገ/ሚካኤል - የምድር ጦር ዋና አዛዥ
2/ ሜ/ጀ ወርቁ ዘውዴ - የፖሊስ ሰራዊት ጠቅላይ አዛዥ
3/ ሜ/ጀ ዓለማየሁ ደስታ - የምድር ጦር ምክትል አዛዥ
4/ ሜ/ጀ ዘውዴ ገብረየስ - የ603ኛ ኮር ዋና አዛዥ
5/ ብ/ጀ ደሣለኝ አበበ - የጦር ኃይሎች አካዳሚ ዋና አዛዥ 6/ ብ/ጀ ሰለሞን በጋሻው - የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ
7/ ብ/ጀ ተስፋ ደስታ - የአየር ኃይል ዘመቻ መኮንን
8 ብ/ጀ እንግዳ ወ/አምላክ - የ606ኛ ኮር ዋና አዛዥ /ሁአሰ 9/ ብ/ጀ እርቅይሁን ባይሣ - የ607ኛ ኮር ዋና አዛዥ /ሁአሰ 10/ ብ/ጀ ነጋሽ ወልደየስ - የ 608ኛ ኮር ዋና አዛዥ /ሁአሰ
11/ ብ/ጀ ገናናው መንግሥቴ - የ6ኛው አየር ምድር ዋና አዛዥ /ሁአሰ
12 ብ/ጀ ተስፋዬ ትርፌ - በአገር መከላከያ ሚኒስቴር ዘመቻ መኮንን

መፈንቅለ መንግስቱን ለማክሸፍ በተንቀሳቀሰው በሻንበል መንግስቱ ገመቹ በተመራው የልዩ ጥበቃ ብርጌድ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ ። በመጨረሻም ከአንድ አመት የጦር ፍ/ቤት ሂደት በኃላ ግንቦት 13/1982 ዓ.ም በፖለቲካዊ ውሳኔ ተረሸኑ ።

የሁአሠ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ደምሴ ቡልቶ የመሩት የአስመራው የመፈንቅለ መንግስቱን የሶስት ቀናት እድሜ አስቆጥሮ ነበር ። ሙከራው መክሸፋ ተከትሎ የ102 ኛ አየር ወለድ ወታደሮች ጀነራል ደምሴን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ መኮንኖችን በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት እየደበደበና በጭካኔ እናነቀ በዘፈቀደ ፈጃቸው ።

የዘመቻ መምሪያ ዋና ኃላፊ የነበሩት ሜ/ጀ አበራ አበበ መፈንቅለ መንግስቱ ከተካሄደበት መከላከያ ሚኒስቴር ግቢ አጥር ዘሎ አምልጠው ለወራት ሲፈለጉ ከቆየ በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኝ የዘመዱ ቤት ውስጥ ተደብቀው ቆይተው በጥቆማ ፖሊሶች ደርሰውባቸው ቤቱ ሲከበብ ሜ/ጀ አበራ አጥር ዘሎ ለማምለጥ ሲሞክሩ በተተኮሰባቸው ጥይት ተገደሉ ።

መቺ ሀይል ከአስመራ በአንቶኖቭ ጭነው አዲስ አበባ የመጡት ሜ/ጀ ቁምላቸው ደጀኔ የነገሮች መበላሸትና የግንኙነት መስመር ስለተቋረጠባቸው ተሠውረው በመቆየት ከሀገር በሙውጣት በመጨረሻ አሜሪካን ገቡ ። ዋና ተዋናይ ሆነው ብቸኛ በህይወት የተረፋ ጀነራልም መኮንንም እሳቸው ብቻ ናቸው ።

ከሁለተኛው አብዮታዊው ሰራዊት ዋና አዛዥ ሜ/ጀ ደምሴ ቡልቶ ጋር በአስመራ ከተማ በ102ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር ህይወታቸው በአሰቃቂ ና በዘፈቀደ ሁኔታ ህይወታቸውን ያጡት ስመጥር ጀነራሎች እና ሌሎች መኮንኖች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦

1/ ብ/ጀ አፈወርቅ ወ/ሚካኤል = የኤርትራ ክ/ሃገር የአስቸኳይ ጊዜ ዋና አስተዳዳሪ
2/ ብ/ጀ ታዬ ባላኪር = የኤርትራ ክ/ሃገር አቢዮታዊ ፖሊስ ዋና አዛዥ
3/ ብ/ጀ ታደሰ ተሰማ = የሁአሰ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
4/ ብ/ጀ ወርቁ ቸርነት = የሁአሰ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ
5/ ብ/ጀ ንጉሴ ዘርጋው = የአስመራ አየር ኃይል ዋና አዛዥ
6/ ብ/ጀ ከበደ መሀሪ = የሁአሰ ድርጅት መምሪያ ኃላፊ
7/ብ/ጀ ተገኔ በቀለ = የኤርትራ ክ/ሃገር የአስቸኳይ ጊዜ አስተዳደር ዘመቻ መኮንን
8/ ብ/ጀ ከተማ አይተንፍሱ = የ 606ኛ ኮር ዋና አዛዥ
9/ ብ/ጀ ከበደ ወ/ጻዲቅ = የ 606ኛ ኮር ዋና ም/አዛዥ
10/ ብ/ጀ ሰለሞን ደሳለኝ = የ 102ኛ አየር ወለድ ክ/ጦር ዋና አዛዥ
11/ ዶ/ር ኮሎኔል ጌታቸው አወቀ = የሁአሰ ሆስፒታል ሜዲካል ዳሬክተር
12/ ኮሎኔል መስፍን አሰፋ = የ2ኛ ሜካናይዝድ ክ/ጦር አዛዥ
13/ ኮሎኔል ፈቃደ እንግዳ = የሁአሰ ዘመቻ መምሪያ ረ/ኃላፊ
14/ ሌ/ኮ ዘርአይ እቁባአብ = የሁአሰ ቀዳሚ መምሪያ ፖለቲካ ኃላፊ
15/ ሌ/ኮ ዮሀንስ ገብረማሪያም = የመከላከያ ቀዳሚ መምሪያ ወታደራዊ መረጃ ኃላፊ
16/ ሻለቃ ካሳ ፈረደ = የሁአሰ መሀንዲስ መምሪያ ኃላፊ
17/ ሻለቃ ሚካኤል ማርቦ = የ 2ኛ ታንከኛ ብርጌድ ፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ
18/ ሻምበል ጌታሁን ግርማ = የሁአሰ ዋና አዛዥ ልዩ ረዳት መምሪያ ኃላፊ

ይህ ሁሉ የጦር ጠበብቶች እልቂትም እንዲህም በመቶዎች የሚቆጠሩ መኮንኖች የጅምላ እስር ግዙፋን ሰራዊት ያለ እውነተኛ እና ልምድ ያለው መሪ በማስቀረት በአጭር ጌዜ ውስጥ ሰራዊቱን ሙሉ ለሙሉ ለአስከፊ ውድቀት ዳርጎታል ።

ፈጣሪ የሟች መኮንኖችን ነፍስ ይማር 🙏

ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ከልጃቸው ሳህለሥላሴ ኃይለሥላሴና ከልጅ ልጃቸው ልዕልት ሰብለ ደስታ ጋር በኤስ ኤስ ዩናይትድ ስቴትስ የባህር መርከብ ላይ ሆነው ፤ ግንቦት 17 ቀን 1946 ዓ...
15/05/2026

ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ከልጃቸው ሳህለሥላሴ ኃይለሥላሴና ከልጅ ልጃቸው ልዕልት ሰብለ ደስታ ጋር በኤስ ኤስ ዩናይትድ ስቴትስ የባህር መርከብ ላይ ሆነው ፤ ግንቦት 17 ቀን 1946 ዓ.ም (ኒውዮርክ)

His Majesty Emperor Haile Selassie I, with his son Sahle Selassie Haile Selassie and his granddaughter Princess Seble Desta, on board the SS United States; May 24, 1954.

በእግዚአብሔር ኃይል ኢትዮጵያ በአንድነቷና በነፃነቷለዘለዓለም ትኖራለች!!!📌 የሀገር ባለውለታ!" አስራት የሚባል ጠበል ፈልቋል ሲሉኝ ወደዚህ መጣሁ!" ዝናቸውን የሠማ ታካሚ" አፍሪካም እንዲ...
14/05/2026

በእግዚአብሔር ኃይል

ኢትዮጵያ በአንድነቷና በነፃነቷ

ለዘለዓለም ትኖራለች!!!

📌 የሀገር ባለውለታ!

" አስራት የሚባል ጠበል ፈልቋል ሲሉኝ ወደዚህ መጣሁ!"

ዝናቸውን የሠማ ታካሚ

" አፍሪካም እንዲህ አይነት ሠው አላት እንዴ የሚያስብሉ የሚያስመኩና የሠራተኛ ሠራተኛ ነበሩ"

የቀድሞው ፓትርያርክ ብፁህ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ

ትውልዳቸው በሠኔ 12 1920 በአዲስ አበባ ከተማ ነው።

በ3 ዓመታቸው ወደ ድሬዳዋ ከተማ በመጓዝ የቤተክርስቲያን ትምህርታቸውን ተምረው ከዚያም ወደ ፈረንሳይ ትምህርት ቤት በመግባት ትምህርታቸውን ለመከታተል በሚዘጋጁበት ወቅት ፋሺስት ጣልያን ሀገራችንን ወረረች።

ከነፃነት በኋላም ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት በመቀጠል ባሳዩት የትምህርት ብልጫ የከፍተኛ ትምህርት ዕድል አግኝተው ወደ ግብፅ አሌክሳንድሪያ ተጓዙ።

በዚያም የእንግሊዝ ዩኒቨርስቲዎች ለመግባት የሚሠጠውን የሁለት ዓመት ትምህርትም በአንድ ዓመት በማጠናቀቅ ወደ ኤደንብራ ዩኒቨርስቲ በመግባት የሕክምና ትምህርታቸውን ተከታተሉ።

በልዕልት ፀሃይ ሆስፒታል ሥራቸውን የጀመሩ ሲሆን ከአምስት ዓመታት በኋላ እንደገና ወደ እንግሊዝ በመጓዝ በሮያል ኮሌጅ ኦፍ ሰርጀንስ በቀዶ ሕክምና ልዩ ትምህርት ተምረዋል።

በጥቁር አንበሳ በልዕልት ፀሃይ ሆስፒታል ከ30 ዓመት በላይ በቀዶ ሕክምና የሠሩ ሲሆን

የቀድሞው የኃይለሥላሴ የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የሕክምና ፋካሊቲ ዲን ነበሩ።

የልዕልት ፀሃይ የአሁኑ (ጦር ኃይሎች) ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ በመሆንም አገልግለዋል።

በሌሎች በርካታ ቦታዎችም ያገለገሉ ሲሆን ለዚህ አገልግሎታቸውም የተለያዩ ሽልማቶችን ያገኙትና ለብዙ ዓመታት ለበሽታ አለቃው የነበሩት ......

ዕውቁ የሕክምና ባለሙያ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ

የጎጃሙ ራስ ሃይሉ ተክለ ሃይማኖት / Ras Hailu Tekle Haimanot of Gojjam
13/05/2026

የጎጃሙ ራስ ሃይሉ ተክለ ሃይማኖት / Ras Hailu Tekle Haimanot of Gojjam

ልዕልት ፀሐይ ኃይለሥላሴ Princess Tsehai Haile Selassie.የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት ነርስ እንዲሁም በሬዲዮ ሞገድ የመጀመሪያዋ የእንግሊዘኛ ቋንቋ ተናጋሪ ፤ የግርማዊ ቀዳማዊ ...
12/05/2026

ልዕልት ፀሐይ ኃይለሥላሴ
Princess Tsehai Haile Selassie.

የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት ነርስ እንዲሁም በሬዲዮ ሞገድ የመጀመሪያዋ የእንግሊዘኛ ቋንቋ ተናጋሪ ፤ የግርማዊ ቀዳማዊ ኘፄ ኃይለሥላሴ እና የእቴጌ መነን አስፋው አራተኛ ልጅ ፤

(ጥቅምት 1912 --- ነሐሴ 1934 ዓ.ም)

ዛሬ ሚያዝያ 30 የዓለም ዓቀፉ የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ  ቀን ነው ሐምሌ 1 ቀን 1927 ዓመተ ምህረት የተመሠረተው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የጄኔቫውን ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ዓለ...
08/05/2026

ዛሬ ሚያዝያ 30 የዓለም ዓቀፉ የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ ቀን ነው

ሐምሌ 1 ቀን 1927 ዓመተ ምህረት የተመሠረተው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የጄኔቫውን ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ዓለም አቀፋዊ ዕውቅናን ከዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ማኅበር አግኝቶ 38ኛው አባል ሆኗል።

ይህ ከመሆኑ ብዙ ዓመታት አስቀድሞ ከዓድዋ ጦርነት መንፈቅ ጊዜ ያህል በኋላ የሩሲያ የቀይ መስቀል አባላት በጄኔራል ሽዊደፍን መሪነት ወደ አገራችን መጥተው የሠጡትን የሕክምና ስራ ካዩ በኋላ ንጉሡና እቴጌይቱ የቀይ መስቀል ማህበር ዓላማና ተግባርን በሚገባ አውቀውታል።

ከዚያን ጊዜ ወዲህ ማለትም በ1889 ዓመተ ምህረት ጀምሮ የቀይ መስቀል ስም በአዲስ አበባ ከተማ የታወቀ ነበር።

በ1899 ንጉሥ ምኒልክ ጥቅምት 12,27 እና ኅዳር 18 ቀን ለሩሲያው ንጉሥና ባለቤታቸው የቀይ መስቀልን መመሥረታቸውን ሶስት ደብዳቤዎችን ፅፈው ነበር። እቴጌ ጣይቱም የማህበሩ የበላይ ጠባቂ ለመሆን መፍቀዳቸውንም ገልፀዋል።

ከእቴጌ ደብዳቤዎች አንዱም ......

እቴጌ ጣይቱ ብርሃን ዘኢትዮጵያ

ይህንን ደብዳቤ ለሚያይ ሕዝብ ሁሉ ሠላምታዬን እሠጣለሁ።

ለክርስቲያን ፥ ለተጎዱም ሕዝብ ለነዳያን ፥ ለቆሰሉም ብርቱ ሕመም ለታመሙም ሕዝብና ሠራዊት የፍቅር የመልካም ሥርዓትና የርኅራኄ ርዳታ ለማሳየት ስላሰብን ይህንንም የርኅራኄ መልካም ምግባር ለመፈፀም በመንግሥታችን በኢትዮጵያ የቀይ መስቀል ማኅበር ለመትከል ወደድን።

በእውነተኛ ልብ የተከልነው የቀይ መስቀል ማኅበር እግዚአብሔር ለመጠበቅ ስላበቃን ማኅበራችንን ለረዳ ለዶክተር ኩርት ሂርትሰቡርህ በከበረው ቀይ መስቀል ንሻኖች አክብረን ሸልመነዋል። ይህንንም ንሻን በደረቱ እንዲይዘው ፈቅደንለታል።

ሰኔ 9 ቀን 1899 ዓመተ ምሕረት አዲስ አበባ ከተማ ተጻፈ።

Address

Mozambique Street, Tselere Building
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኮረማሽ-Koremash posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ኮረማሽ-Koremash:

Share