11/04/2026
🪸🪸🪸🪸🪸
አክሱምን የማውቃት በጣም የምንወደው አስተማሪችን ፀጋ-ብርሃን ወ/ጊዮርጊስ ባዘጋጀልን ጉዞ ነው፡፡ ይህን ጉዞ ያደረግነው 60 ምናምን የምንሆን የ2009 ባች የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ትመህርት ክፍል ተማሪዎች ነን፡፡ ጉዞውን ያደረግነው መጋቢት/ሚያዚ 2011 ነው፡፡ እውነት ለመናገር የትግራይ ህዝብ የዋህ እና ኩሩ ኢትዮጵያዊ፣ እንግዳ አክባሪ መሆኑነ መረዳት ችያለው፡፡ ከተማሪወቹ ውስጥ 5 ሙስሊሞች ነበርን (እኔ፣ አህመድ፣ ቡላላ፣ ፈይሳ እና ሙሃመድ) ፤ ጾመኞች ነን፡፡ በምሽቱ ወጥተን ምግብ ለማሰራት አንድ የማናውቀው የመቀሌ ልጅ እንደ የግል ጠባቂ/ጋርድ ሳንጠይቀው አጅቦን ምግባችንን አሰርተን ካምፓስ ገባን (መቀሌ)፡፡ በቃ ወርቅ ኢትዮጵያዊ ናቸው፡፡
ግን የማንክደው ሃቅ አለ፡፡ በቃ ወንበዴዎች አሉ፤ በተለይ አክሱም፡፡ አክሱም ዓስር ሰላትን ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ አንደሌላው ቦታ መስሎኝ ልሰግድ ሳር ቦታ ልብሴን አንጥፌ፣ ሃርሜ ቆምኩኝ ሙሃመድ ቃዲ ሊሰግድ ተከተለኝ፤ ሰላታችንን አሳጥረን ሰገድን፤ ያው ሙሳፊሮች አይደለን፡፡ ከጨረስን በኋላ ቀና እንላለን በሙሉ የዶርሙ ተማሪ ሁሉ እሪሪ እያለ በኮሪደር ዘልቆ ይመለከተናል፡፡ ምንድን ነው ይህ ነገር ዩኒቨርስቲ ግቢ ውስጥ መስገድ አይቻልም እንዴ እያልኩ ማሰብ ጀመርኩ፤ ከዛ በፊት ጅምላ ክልከላ እንዳለ አልሰማውም፤ ከመረጃ እርቄአለሁኝ፡፡ የሆነው ሁኖ እንግዳ መሆናችንን አይተው መሰለኝ ማንም ሰው አልጠየቀንም፡፡ አንድ የመውቀው የዩኒቨርስቲው ተማሪ ነበር (ገብረ-ህይዎት) መስገድ አይቻልም፤ ተከልክሎ ነው ብሎ ነገረኝ፡፡ ወገኖቼ፣ አክሱም እንደማንኛውም ከተማ፣ መጠጥ የሚሸጥባት፣ ጭፈራ ቤቶችን የምታስተናግድ፣ ለክርስትና እንኳ በሙሉ እጅ የማይሰጡ አንዳድ አካል ያለባት ከተማ ናት፡፡
እናም መስጅድ መኖሩ እንደምትባለው ቅድስት ከተማም ከሆነች ቅድስነቷ አይጠፋም፡፡ ጀሩሳሌም ውስጥ ያሉትን ቤተ-ክርስቲያኖች እና መስጅዶች ቅርበት፣ ሃገራችን ውስጥ ደጀን ከተማ ውስጥ ያለው የመስጅድ እና የቤተክርስቲያን እርቀት እንዲሁም ራጉኤልን እና አነዋርን እናስብ፡፡ የደጀኑማ ዘይገርም ነው፡፡ የእምነትህን ትእዛዝ ለምን ትፈጽማልህ ተብሎ ግድያ፣ እንግልት፣ ቁርኣንን መቅደድ እኮ የትም አያደርስም፡፡ እምነቱን የሚወድ እና የሚያከብር ሰው ክርስቲያን ይሁን ሙስሊም፣ የሁዳ ይሁንም ዛፍ አምላኪ የሌሎችን ድንበር መጣስ፣ መተናኮል፣ መጋፋት፣ ግፍ መፈጸም አይቀናውመ በቃ ደስ አይለውም፡፡ እምነት እኮ ቀሚስ መልበስ፣ ጺም ማሳደግ፣ ሱሪ ማሰጠር፣ ማተብ ማሰር፣ ነጠላ መልበስ ብቻ አይደለም፡፡ ለምንስ የሌሎችን መብት እንጋፋለን? እምነታችን አዘዘን? እረ ወገኖቼ እኔንም ጨምሮ ልብ የምንገዛበት ጌዜ መች ይሁን? ልብ መግዛት እኮ ያን ያክል ዋጋ አያስከፍልም፡፡ ይህችን ምድር መቼም ወረሾች አየደለንምኮ፡፡
https://t.me/MuradeHassen