07/08/2026
ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም!🤲
መገኛ
ዲማ በምስራቅ ጎጃም ዞን በእነማይ ወረዳ ከአዲስ አበባ ወደ ባህር ዳር በሚወስደው ዋና መንገድ ከጠልማ ቀበሌ ምስራቅ አቅጣጫ 12 ኪ.ሜ ገባ ብሎ ይገኛል።
ስያሜ
የገዳሙ ስያሜ መነሻ ደብረ ድማህ የሚለው ስም ሲሆን ትርጓሜዉም ራስ /ጭንቅላት/ ማለት ነው፡፡ ይህም በቀደመው ጊዜ ዲማ የጎጃም ማዕከል ነበር የሚለውን ለማመላከት ነው። በሌላ በኩል ዲማ ቀይ ማለት ነው።
የተመሰረተበት ዘመን
ዲማ ጊዮርጊስ የተመሰረተው በ1297ዓ.ም የቀድሞ ስማቸው አባ በኪሞስ በኋላ ግን ተከስተ ብርሃን በተባሉ የሃይማኖት አባት አማካኝነት ነው።
የቅርስ ሀብት
የአጼ ይስሃቅ የወርቅ ጫማ፣ የአጼ ዮሐንስ የወርቅ ዘውድና የወርቅ መስቀል፣ የእባብ ቅርፅ ያለዉ የወርቅ ዘንግ፣ በስዕል የተንቆጠቆጡ የብራና መጻሕፍት፣ የንጉሥ ተክለ ኃይማኖት ጦርና ጋሻ፣ የራስ መኮንን ካባ እና ሌሎች በዋጋ የማይተመኑ ውድ ቅርሶች ባለቤት ነው።
አራቱ ጉባኤዎች እና ሴቶች
በዲማ ቅኔን ጨምሮ የአራቱ ጉባኤዎች ትምህርት ይሰጣል። ከወንዶች በተጨማሪ በእማሆይ ህሪት ደባስ መምህርነት ሴቶች ለብቻቸው የቅኔ ትምህርት ይከታተላሉ።
ታዋቂ ኢትዮጵያውያን
ዲማ የፍቅር እስከ መቃብር ደራሲ ክቡር ዶክተር ሀዲስ አለማየሁ የተማሩበት እና በመጽሐፋቸው መቸት ያደረጉበት ቦታ ነው፡፡ ታላቁ ሊቅ መላከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ እና ሌሎች በርካታ ታዋቂ ኢትዮጵያውያን በዲማ ተምረዋል።
ክብረ በዓል
ታህሳስ 8፣ ጥር 18፣ ሚያዝያ 23 በዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም ዋና የንግሥ በዓል መከበሪያ ቀናት ናቸው።
ምንጭ፦ ፌስቡክ ላይ የተገኘ ነዉ