14/05/2026
እናስታውስዎ!
በአብዛኞቹ ከተሞች የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር የተቀመጠው ቀነ ገደብ ዛሬ ይጠናቀቃል!
ባንካችን ያዘጋጀውን የበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) በመጠቀም አሁኑኑኑ ያስተሳስሩ።
********
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ (ብሔራዊ መታወቂያ) ጋር የማስተሳሰር ስራን በተመለከተ በቅርቡ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት በሀረር፣ አዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ አስተዳደር፣ ባህርዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ደብረብርሃን፣ ኮምቦልቻ፣ ሀዋሳ፣ አርባ ምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ሆሳዕና፣ ወራቤ፣ ቡታጂራ፣ ወልቂጤ፣ ሸገር፣ ጅማ፣ አዳማ፣ ሻሸመኔ፣ ቢሾፍቱ፣ ባቱ፣ አምቦ፣ መቐለ፣ አክሱም፣ ዓዲግራት፣ ጋምቤላ እና አሶሳ ከተሞች የሚገኙ ደንበኞች እስከ ዛሬ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም (May 14, 2026) ድረስ ሂሳባቸውን ከፋይዳ ቁጥር (ብሔራዊ መታወቂያ) ጋር ማስተሳሰር እና ማጠናቀቅ ይኖርባቸዋል።
በተቀሩት የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የባንክ ቅርንጫፍ ደንበኞች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (July 07, 2026) ድረስ ማጠናቀቅ ይኖርባቸዋል።
በመሆኑም ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያቸው ጋር ያላጣመሩ ደንበኞች የባንክ አገልግሎት የማያገኙ መሆኑን ተረድታችሁ፣ በባንኩ ቅርንጫፎች በመገኘት ወይም ባንካችን ያዘጋጀውን የበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) በመጠቀም ከተጠቀሰው ቀነ ገደብ በፊት በማጣመር ካላስፈላጊ የአገልግሎት መስተጓጎል ራሳችሁን እንድትጠብቁ እናሳስባለን።
ስለትብብራችሁ በቅድሚያ እናመሰግናለን!
********
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!