Ethiopian Hotel Professionals Association -EHPA

Ethiopian Hotel Professionals Association -EHPA This Association is unique in its kind and aims to empower it's members & contribute to the sector.

Ethiopian Hotel Professionals’ Association
EHPA Is The First And Very Unique Professional Network In Ethiopia Which Is Designed To Encourage All Hospitality Professionals To Discuss Common Issues, To Share Experiences, Communicate Opportunities, Contribute To The Sector And More,

27/12/2024
19/12/2024

ለአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ የሚገቡ እንግዶችን ለመቀበል ከወዲሁ ተዘጋጅተናል- የአዲስ አበባ ሆቴሎች
አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 10/2017(ኢዜአ)፦ በ38ኛው የአፍሪካ ኀብረት የመሪዎች ጉባኤ የሚሳተፉ እንግዶችን ለመቀበል አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጋቸውን ኢዜአ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ሆቴሎች ገለጹ፡፡
ኢትዮጵያ የፊታችን የካቲት መጀመሪያ ሳምንት በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ሁሉን አቀፍ ቅድመ ዝግጅት እያደረገች ነው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉባዔውን የኢትዮጵያን ገጽታና የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማዕከልነት በሚያሳድግ መልኩ ለማስተናገድ ቅድመ ዝግጅት ስለማድረጉ ማስታወቁ ይታወሳል።
በጉባዔው ታዳሚያን እንግዶችን በመቀበል ወሳኝ ድርሻ ከሚኖራቸው ባለድርሻ የግል ተቋማት መካከል የሆቴልና መሰል አገልግሎት ዘርፍ ይገኝበታል።
በአዲስ አበባ ከተማ የአገልግሎት አሰጣጣጥና የሆቴል ፋሲሊቲዎች መሰረት በማድረግ 42 ሆቴሎች እንግዶቹን እንዲያስተናገዱ መመረጣቸውን የአዲስ አበባ ሆቴል እና ቱሪዝም ባለሙያዎች ማህበር መረጃ ያሳያል።
ኢዜአ ያነጋገራቸው የኢንተርሌግዤሪ እና የካፒታል ሆቴሎች እንደሚሉት በሕብረቱ ጉባዔ ለመሳተፍ የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቀዋል።
የካፒታል ሆቴል ስራ አስኪያጅ ተስፉ ፍጹም እንደሚሉት ሆቴሉ የኢትዮጵያን እንግዳ ተቀባይነት እሴት የጠበቀና የደንበኞችን እርካታ ያገናዘበ አገልግሎት ለመስጠት ተዘጋጀቷል።
ደንበኞቻቸውን ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ከመቀበል ጀምሮ ደህንነታቸው በተጠበቀና በሚመጥናቸው ደረጃ እንዲስተናገዱ ለማድረግ እንደተዘጋጀ ነው ያነሱት።
የኢንተርሌግዤሪ ሆቴል ምክትል ስራ አስኪያጅ በሱፈቃድ ደባይ በበኩላቸው፤ ደረጃውን የጠበቀ አቀባበልና የሆቴል መስተንግዶ ለመስጠት ከወዲሁ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ሆቴል እና ቱሪዝም ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት አሸናፊ ሙሉጌታ፤ ለእንግዶች ቆይታና ምቾት የዘርፉ ባለሙያዎች ያላቸው ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል።
እንግዶችን አያያዝና መስተንግዶ ለሀገር ገጽታ በሚያጎላ መልኩ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
በዚህም አገልግሎት አሰጣጣጥን፣ መገልገያ ቁሳቁሶች እና ሆቴሉ ውስጥ ያሉ ፋሲሊቲዎች መሰረት በማድረግ በመዲናዋ የሚገኙ 42 ሆቴሎች እንግዶቹን እንዲያስተናገዱ መመረጣቸውን ጠቅሰዋል።
38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ የካቲት 8 እና 9 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲሁም 46ኛው የህብረቱ የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ደግሞ የካቲት 5 እና 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

በማህበራት ፣ በሚዲያ እና በህዝቡ ከሚነሱ የሰራተኛው ጥያቄዎች ውስጥ ግንባር ቀደሙ የግብር (ታክስ) ጉዳይ ነው፡፡በተለይም በታማኝነት ከወር ደመወዙ ግማሽ ያህሉ የሚቆረጥበት ሰራተኛ ህይወት ...
15/12/2024

በማህበራት ፣ በሚዲያ እና በህዝቡ ከሚነሱ የሰራተኛው ጥያቄዎች ውስጥ ግንባር ቀደሙ የግብር (ታክስ) ጉዳይ ነው፡፡

በተለይም በታማኝነት ከወር ደመወዙ ግማሽ ያህሉ የሚቆረጥበት ሰራተኛ ህይወት ከጊዜ ወደ ጊዜ የበለጠ ችግረኛ እንዲሆን እያደረገው ነው፡፡

በሚበላው፣ በሚጠጣው የተጨማሪ እሴት ታክስ የሚከፍለው ሰራተኛ ጉዳይ ተደጋግሞ በመንግስት እንዲታይ ቢጠየቅም ምላሽ አላገኘም፡፡

The Current Dollar Exchange Dynamics: An Opportunity Rather Than a Threat for Hotel OwnersIn the present economic scenar...
11/12/2024

The Current Dollar Exchange Dynamics: An Opportunity Rather Than a Threat for Hotel Owners
In the present economic scenario, the fluctuations in the dollar exchange rate should be viewed as an opportunity rather than a cause for concern. For hotel owners, this shift represents a chance to significantly increase revenue without necessarily enhancing services compared to previous offerings.
Revenue Growth and Its Contributors
The increase in revenue is not solely attributed to currency exchange adjustments but also to the collective efforts of employees. It is evident that the workforce plays a crucial role in achieving profitability, earning their fair share of recognition and benefits.
The Role of Professional Communities
Hotel industry associations, which have traditionally represented the voice of hotel owners, must now act as a bridge to present constructive ideas to stakeholders. This should be done while ensuring professionals within the sector are fairly compensated and supported, as their contributions are critical to the industry's success.
Stakeholder Benefits
1. Owners: The increase in revenue highlights the indispensable role of employees. By sharing a portion of these gains with the workforce, owners can foster motivation and loyalty, further enhancing productivity and service quality. A collaborative approach between owners and employees ensures sustainable growth.
2. Government: A harmonious relationship between employers and employees is pivotal to national stability. Additionally, higher revenues for hotel owners translate to increased tax contributions, benefitting public welfare.
3. Guests: Exceptional service originates from satisfied and well-compensated staff. Happy employees are more likely to deliver heartfelt and memorable service, ensuring guests become loyal patrons and indirectly boosting the establishment's profitability.
Challenges and Their Implications
However, achieving this balance is not without its hurdles:
• Owner Resistance: Some owners may be hesitant to embrace change and adjust employee benefits.
• Talent Drain: Employees may leave for better opportunities elsewhere, affecting service continuity.
• Misalignment in Associations: Some industry leaders prioritize personal gain over collective benefits.
• Unstable Industry Climate: A lack of standardization and frequent challenges create an unpredictable environment for stakeholders.
The Way Forward
The solution lies in acknowledging the shared responsibility among all stakeholders. Industry associations should act proactively, facilitating dialogue between owners and employees. Transparent and solution-focused discussions must address core challenges, aligning interests to ensure mutual benefits.
Call to Action
By fostering a culture of collaboration and fairness, the hospitality industry can transform these challenges into opportunities, ensuring sustainable growth for all involved.

አሁን ባለው የዶላር ምንዛሬ መለወጥ ለሆቴል ባለቤቶች  ዕድል እንጂ ስጋት እንዳልሆነ ይታወቃል (Opportunity  vs Threat  approach ) ።ይሄ ማለት አንድ የሆቴል ባለቤት ከዚ...
11/12/2024

አሁን ባለው የዶላር ምንዛሬ መለወጥ ለሆቴል ባለቤቶች ዕድል እንጂ ስጋት እንዳልሆነ ይታወቃል (Opportunity vs Threat approach ) ።ይሄ ማለት አንድ የሆቴል ባለቤት ከዚህ በፊት ይሰጥበት የነበረውን አገልግሎት ሳይጨምር ገቢው በአስገራሚ ሁኔታ ተመንድጓል ማለት ነው። የገቢ መጨመር ተጽእኖ በዶላር ለውጡ ብቻ ሳይሆን የአንበሳውን ድርሻ የሚጫወቱት ሠራተኞች መሆናቻው እውነታው አይካድም።
ከዚህ በፊት የሆቴል ባለሙያዎች ማኅበራት ለባለሀብቱ ድምጽ እንደሆነ ሁሉ ዛሬ ደሞ ሀገራችን እና ሠራተኞች ያሉበትን ሁኔታ በማጤን ይሄን ከፍ ያለ ሃሳብ ለባለድርሻ አካላት ማቅረብ እና የባለሙያውን የልፉት ዋጋ እንዲያገኝ ማስደረግ ዋና ተግባር ሊሆን ይገባል ብለን እናምናለን ፡፡ ይህ ሃሳብ ሁሉንም ባለድርሻ አካላትን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሃሳብ መሆኑን ለማሳየት ያክል ፡-
ባለሃብቱ ( የሆቴሎች ባለቤት) ባለሀብቱ ገቢው መጨመሩን ለሰከንድ ከሠራተኛው አይደበቅም። በዚህም ሁኔታ ባለሀብቱ ሠራተኞቹን ገቢው የጨመረው በሠራተኞቹ መሆኑን አምኖ ሠራተኞችን ሰብስቦ ይሄ ውጤት የእነሱ መሆኑን እውቅና ሰጥቶ ትርጉም ያለው ጭማሪ ካደረገ በድጋሚ ባለሀብቱ ካሰበው በላይ ገቢው እንደሚጨምር ለሰከንድ መጠራጠር የለበትም።
ሠራተኞች የተነቃቁና በሚከፈላቸው ክፍያ የተደሰቱ ሲሆኑ ለድርጅቱ ያላቸው የባለቤትነት ስሜት በአሰገራሚ ሁኔታ ያድጋል ይመነደግማል።
መንግስት ፤ በአሠሪና ሠራተኛ መካከል ሰላሚዊ ግንኙነት መፈጠሩ በሌላ መንገድ ለሀገር ሰላም ያለው ሚና አዎንታዊ ነው። በሌላም መንገድ ገቢው የጨመረ ባለሀብት የሚከፍለው የግብር መጠንም በዛው ልክ ይመነደጋል።
እንግዶች፤ የሆቴል አገልግሎት የሚሰጠው በሰው ነው ፤ ሰው ስንል ሰራተኞቹ ናቸው ፡፡ በስራው እና በክፍያው ደስተኛ የሆነ ሰራተኛ ለእንግዶች ከልብ የመነጨ አገልግሎትን ለመስጠት ቀን ከሌት ደፋ ቀና ማለቱ እሙን ነው ፡፡ እንግዶች የላቀ አገልግሎትን ካገኙ የድርጅቱ ታማኝ እንግዳ ሆኑ ማለት ነው ይህ ደግሞ ቀላቂ ትርፋማነትን ያመጣል ፡፡
ይሁን እንጂ ለምን ይህ ለውጥ ትኩረት ተነፈገው ፤ ተግዳሮቶቹስ ምን ምን ናቸው ስንል
የባለሀብቱ አዎንታዊ ምላሽ አለመስጠት (Owners resistant)
ሰራተኞች ስራቸውን ሰርተው መብታቸውን ከመጠየቅ ይልቅ ከአንዱ ሆቴል ወደሌላ መፍለስ(Talent drainage )
ማህበራቱ እና መሪዎችቸው ከባለሙያው ጥቅም ይልቅ ለግል ጥቅም ያደሩ መሆናቸው ( )
ባለድርሻ አካላት እና የመንግስት ተቋማት ትኩረት መንፈግ
ያልተረጋጋ ኢንደስትሪ መስፈን (existence of unrest Industry )
እና የመሳሰሉት ይገኙበታል ፡፡
ይሁን እንጂ የችግሩ ቀፈት ቀማሽ ባለሙያው እንደመሆኑ መፍትሄውም ከባለሙያው መንጪቶ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ማድረግ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ተግባር ነው ፡፡
ይህ ማኀበር ላለፉት 25 ዓመታት የባለሙያውን ችግር ለመቅረፍ ደፋ ቀና ሲል የኖረ እና እጅግ በጣም ተጽእኖ ፈጣሪ እና ህጋዊ ማኅበር እንደመሆኑ መጠን ከበርካታ ተቋማት ሠራተኞች የሠራተኞች የእርካታ ዳሰሳ አጥንቶ የውውይት መድረክ ለማዘጋጀት አቅዱል ፡፡ ስለሆነም ግልጽ፣ ችግር ፈቺ ውይይት ለማዘጋጀት ያሰብን በመሆኑ ሁሉም ባለሙያ አሁናዊ መሰረታዊ ችግሮች እና ተግዳሮቶቹን በማንሳት በመወያየት የድርሻውን እንዲወጣ ስንል ትሪ እናስተላልፋለን፡፡

የኢሆባሙ የተመሰረተው የሆቴል ባለሙያዎች በተደራጀ መልክ ህጋዊ ሂደት ተከትለው ለመብታቸው ፣ ለሙያቸው ፣ ለጥቅማቸው ፣ ለህልውናቸው ፣ ለተሻለ ሙያዊ አገልግሎት ጥራት እና ወዘተ ለማግኘት እ...
08/12/2024

የኢሆባሙ የተመሰረተው የሆቴል ባለሙያዎች በተደራጀ መልክ ህጋዊ ሂደት ተከትለው ለመብታቸው ፣ ለሙያቸው ፣ ለጥቅማቸው ፣ ለህልውናቸው ፣ ለተሻለ ሙያዊ አገልግሎት ጥራት እና ወዘተ ለማግኘት እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህ ማህበር ከተመሰረተ 25 ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን አንግቦ የተነሳውን አላማ ከግብ ለማድረስ ሁሉም የሆቴል ባለሙያዎች የበኩላቸውን መወጣት ይገባቸዋል፡፡ ማህበር (Association) ትልቅ አቅም ያለው አደረጃጀት እንደሆነ ይታወቃል። ስለዚህ የምንፈልገውን ጥያቄያችን ለማሳካት ተሰሚነት ያለውን ጠንካራ እና አንጋፋ ማህበር ማጠናከር ምርጫ የማሰጠው ጉዳይ ነው ።
የኢትዮጵያ የሆቴል ባለሙያዎች ማህበር ትልቅ ሃገራዊ ተቋም እንዲሆንና ለሁሉም የሃገሪቱ የሆቴል ባለሙያዎች ድምፅና ልሳን እንዲሆን የሚፈልግ የሆቴል ባለሙያ ሁሉ ከዳር ቁሞ ከመቆዘምና ሙያዉን ከማማረር ይልቅ የማህበሩ ህጋዊ አባል ሁኖ ማህበሩን ጠንካራ ተቋም በማድረግ ለመብቱ ዘብ መቆምና መጠየቅ ይገባዋል።
አንድን ማህበር ጠንካራና ግዙፍ ከሚያደርጉት የመጀመርያዎቹ ነገሮች አንዱ በስሩ ያሉ አላማዉን በፅኑ የሚደግፉ የማህበሩ አባላት ዋነኞቹ ናቸዉ። በአብዛኛዉ ታዳጊ ሃገራት የሲቪል ማህበራት ጠንካራ ተቋማት እንዲሆኑ አይፈለግም፡፡ እነዚህ ተቋማት ጠንክረዉ ከወጡ መንግስትን የመሞገትና የሰራተኛዉን አላማ ለማስፈፀም በእጅጉ ቅርብ ስለሆኑ ነዉ።
በኢትዮጵያ የሆቴል ባለሙያዎች አሁናዊ ሁኔታ እጅግ ብዙ በሚባሉ የተበጣጠሱ የሙያ ማህበራት መኖራቸዉ የሆቴል ባለሙያዎችን የመከራ ጊዜ አስረዘመዉ እንጂ ለሆቴል ባለሙያዎች ያመጣዉ ተጨባጭ ለዉጥ የለም።
በሃገሪቱ ትልቁን የሰዉ ሃይል የሚሸፍነዉ የሆስፒታሊቲ ኢንደስትሪ እስካሁን አቅምያለው በባለሙያዎቹ የተደገፈ ለመብቱ የሚሟገትለት አንድ ትልቅ ሃገራዊ ተቋም ባለመኖሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ በብዙ ነገሮች ተጎጂ እየሆነ ሙያዉም የሚገባዉን ያክል ሳያድግና ተገቢዉን ክብር ሳያገኝ ቀርቷል ።
ስለሆነም የኢትዮጵያ የሆቴል ባለሙያዎች ማህበርን በደንብ ማደራጀት ፣ትልቅ፣ አንጋፋ የሆቴል ባለሙያዎች ብቸኛ የመሰብሰቢያ ተቋም ማድረግ ለነገ የማይባል ለሁሉም የሆቴል ባለሙያዎች ምርጫ የሌለዉ ተግባር ነዉ። ቁጭ ብለን ማንም መብታችን እንዲያከብርልን አንጠብቅ መብታችን የሚከበረዉ በራሳችን ጥረት ብቻ እና ብቻ ነዉ !! የማህበሩ አድራሻ
• አዲስ አበባ ሜክሲኮ ቡናና ሻይ አጠገብ የሆቴል እና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ግቢ ውስጥ
• ስልክ ቁጥር፡- +251 912430509 Kiflu W/giorgise / +251904424763 Misikr Mamo/ +251 920473015 Ejigu Endeshaw
• ኢሜል :- [email protected]
• page:- Ethiopian Hotel Professionals Association -EHPA
• Telegram Group:- https://t.me/hoteliergroup
• LinkdIn Page:- https://www.linkedin.com/in/ethiopian-hotel-professional-association-

You can view and join right away.

The Voice of Hotel Professionals Together, We Overcome ChallengesThe hospitality industry in Ethiopia is undergoing a si...
05/12/2024

The Voice of Hotel Professionals Together, We Overcome Challenges

The hospitality industry in Ethiopia is undergoing a significant transformation. From navigating post-pandemic recovery to tackling inflation, power outages, and water shortages, hotel professionals are facing challenges that test their resilience daily. Yet, amidst these trials, our determination and passion to provide world-class service remain unwavering.

One of the most pressing challenges today is the underrepresentation of hotel professionals in decision-making processes affecting our sector. Whether it's policy-making, labor rights, or fair working conditions, our voices need to be heard. Many professionals also face limited career growth opportunities and the constant struggle to balance global standards with local realities.

The Ethiopian Hotel Professionals Association (EHPA) exists to bridge these gaps. As an organized body, we aim to amplify your concerns, provide a platform for shared solutions, and drive positive change for all stakeholders in the hospitality industry.

Together, we can influence policies, foster innovation, and ensure that the rights of hotel professionals are respected and valued. Let us be a united force advocating for fair treatment, professional development, and a thriving hospitality sector in Ethiopia.

Be part of the association to keep your rights as a team. https://t.me/hoteliergroup

ድር ቢያብር ሰራተኞች ጥንካሬ የሚያገኙት አንድነት ኖሯቸው ማህበር ሲመሰርቱ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ብቻውን መስራትና መኖር አይችልም ፤ ሲሰራም ሆነ ሲኖር ፤ በችግርም ሆነ በደስታ ወቅት የሚረ...
04/12/2024

ድር ቢያብር
ሰራተኞች ጥንካሬ የሚያገኙት አንድነት ኖሯቸው ማህበር ሲመሰርቱ ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ብቻውን መስራትና መኖር አይችልም ፤ ሲሰራም ሆነ ሲኖር ፤ በችግርም ሆነ በደስታ ወቅት የሚረዳውና አይዞህ የሚለው ሰው ያስፈልገዋል፡፡ በርታ ካሉት ይጠነክራል፡፡ ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ይባል የለ መተባበርን የመሰለ ታላቅ ነገር የለም፡፡ በተለይ ለሆቴል ሰራተኞች፡፡
አንድን ዝሆን ለበቻው ታግለን ለማሸነፍም ሆነ ገፍትረን ለመጣል አንችልም ከየአቅጣጫው ተባብረን ከዘረጠጥነው ግን እንጥለዋለን፡፡ የሰራተኞችንም አንድነት በዚህ ሊመሰል ይችላል፡፡ ከተባበርን እንኳንና አንድ ዝሆን ግዙፍ ተራራ እናፈርሳለን፡፡
ቢሆንም ነገሩ እንዳነጋገሩ ቀላል ላይሆን ይችላል፡፡ ዋናው ነገር ግን ልባዊ ፈቃድና እውነተኛ ፅኑ አላማ ነው፡፡ ታድያ ዛሬ አደራጅተን ያላጠናከርነውን ህብረት ነገ ሊደርስልንና አለኝታ ሊሆነን አይችልም፡፡ ዛሬ በወጉ ያልመሰረቱትና ተባብረው ያልገነቡት ቤት ነገ መኖሪያና መግቢያ ሊሆን አይችልም፡፡ ስለዚህ ከህብረት የበለጠ ነገር የለም ፤ ልባችን አንድ መሆን አለበት ፡፡
ሞተን አውሬ ቢበላን አንሰማም ፤ በቁማችን እየሰማን ቀስ በቀስ ልሰውና ግጠው የሚጨርሱን ግን አሉ ፤ በኛ ጉልበትና ህይወት ይኖራሉ እየቦጨቁን እና እየነጩን እንዳይጨርሱን በአንድነት ቆመን መከላከል አለብን፡፡ ዛሬ የምናቋቁመው ማህበር የስራና የኑሮአችን ዋስትና ነው፡፡ የመብታችን ማስከበሪያና ማረጋገጫ ይሆናል፡፡ በስራ ላይ ብዙ ችግር ይገጥመናል ለዚህ ሁሉ መድህኑ ማህበሩ ነው፡፡
ለነባሮቹ ችግሮች እልባት ለመስጠት አዲስ ዘዴ መፍጠር መቻል አለብን፡፡ ይህ ሴክተር ከኛ ከባለሙያዎቹ የተሻለ ማንም ሊመጣለትና ከአዘቅቱ ሊያወጣው አይችልም፡፡ ለዚህ ሴክተር ማንነታችንንና ህይወታችንን እስከሰጠን ድረስ እና ከእንጀራችንም በላይ መሆኑን ተረድተን ከላሸቀና ከበሰበሰ አስተሳሰብና አመለካከት ብሎም ከስግብግቦች ዝርፌያ ልንታደገው ይገባል፡፡
በሆቴል ሴክተሩ ውስጥ ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገቡ ነገሮችን የሚያውቁ ባለጸጋዎች ጥቂቶች ናቸው፡፡ ከተገተረው ህንፃ ፣ ከቀረጥ ነፃ ከገባው እቃና የመስሪያ መሳሪያ በላይ ለሆቴል ትልቁ ሃብቱ ሰራተኞቹ መሆኑን ተረድተው ለየሁሉም እንደሚገባው የሚያከፋፍሉ ቢሆንም አብዛሃኞቹ ግን የሰራተኛቸውን ላብ በከንቱ እያፈሰሱ በሌላው ላብና ጉልበት ከእባብ ቆዳ የተሰራ ጫማ ፣ ከአዞ ቆዳ የተሰራ ቀበቶ እና ከነብር ቆዳ የተሰራ ሸሚዝ ተጫምተውና ተላብሰው በጫንቃው የተሸከማቸውን ሰራተኛ ሲበድሉና ሲያስለቅሱ ለጉድ ነው፡፡
ሰው ሁልጊዜ ኗሪ አይደለም እንደ እንጨት ተሰባሪ ነው፡፡ ጧት በደህና ወጥተን ማታ በጤና እንደምንመለስ እርግጠኛ ባልሆንበት በዚህ ክፉ ጊዜ እንኳን በሰላሙ ጊዜ ሃብትና ንብረት እንደ ጉድ ያጎርፉላቸው የነበረውን ሠራተኛ አይዞህ ከጎንህ ነን ቢሉት እኛም ምንኛ በተደሰትን ነበር፡፡ በቁማችን ካልተረዳዳንና ካልተሰባሰብን የኛ ሲለፉ መዋል ምንም ፋይዳ የለውም፡፡
በሌላ ሴክተር የሚገኙ ሠራተኞች እርስ በርሳቸው እየተረዳዱ ዛሬ የትና የት ደርሰዋል፡፡ እኛም ይህን ሕብረት አጠንክረን ከቀጠልንበት ከሌሎች ብንበልጥ እንጂ አናንስም፡፡ ምንም የሚቸግረን ነገር አይኖርም እኛ እንኳን ቢያቅተን አይዟችሁ በርቱ የሚለን አይታጣም፡፡
በኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት ተሰባስበን ያንን ክፉ ግዜ ተደጋግፈን ማለፍ እንደቻለን ሁሉ ፤ አሁንም በዚህ በኑሮ ውድነት ምክንያት እየተሰቃየ እና በልቶ ማደር ለከበደው ፣ የቤት ኪራይ ተቸግሮ ከአከራይ ጋር ድብብቆሽ ለሚጫወተው ፣ ለልጆቹ ልብስ እና ጉርስ ያጣ የሆቴል ባለሙያ ደመዎዝ እና መሰል ጥቅማ ጥቅም እንዲከበርለት አለፍ ሲልም ሙያውንም አሁን ካለበት ደረጃ አንድ እርምጃ ከፍ ለማድረግ ፤ የሚመለከታቸው የዘርፉ ባለድርሻ አካላትም ትኩረት ይሰጡት ዘንድ በማህበር ታቅፈን መብታችንን ልናስከብር ይገባል፡፡
በመሆኑም አቅሙ እና ጊዜው ያላችሁ የሆቴል ባለሙያዎች ማህበራዊ ኃላፊነታችሁን ለመወጣት በቦርድ አባልነት ፣ በንዑሳን ኮሚቴ እና መሰል የእናንተን እገዛ በሚያስፈልግ ሃላፊነት ውስጥ በመግባት ለባለሙያው መብት መከበር አስተዋፆ ታደርጉ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ አቅሙ እና ጊዜው ያልፈቀደላችሁ የሆቴል ባለሙያዎች ደግሞ በማህበር ታቅፈን የአባላት ግዴታችንን እየተወጣን እና ስለሙያው አስፈላጊውን ምክክር እያደረግን የሃገራችንን ገፅታ መገንባት ላይ አበክረን እንስራ በማለት መልዕክታችን እናስተላልፋለን ፡፡
የኢትዩጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር
• አዲስ አበባ ሜክሲኮ ቡናና ሻይ አጠገብ የሆቴል እና ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ግቢ ውስጥ
• ስልክ ቁጥር፡- +251 912430509 Ato. Kiflu W/giorgise / +251904424763 Ato. Misikr Mamo/ +251 920473015 Ato. Ejigu Endeshaw
• ኢሜል :- [email protected]
• page:- Ethiopian Hotel Professionals Association -EHPA
• Telegram Group:- https://t.me/hoteliergroup
• LinkdIn Page:- https://www.linkedin.com/in/ethiopian-hotel-professional-association-

You can view and join right away.

Beynouna Village at Lake Beseka a stunningly developed destination!hashtag  hashtaghashtag  hashtaghashtag  hashtaghasht...
01/12/2024

Beynouna Village at Lake Beseka a stunningly developed destination!

hashtag hashtag
hashtag hashtag
hashtag hashtag
hashtag hashtag
hashtag
hashtag

https://p.dw.com/p/4nWxjበዛሬው ዕለት ከጀርመን የአማርኛ ድምፅ  ጋር ሰለኢትዩጵያ ሆቴሎችና ሬስቶራንቶች ዩኒፎርም አለባበስና ሰለኢትዩጵያ የሆቴል አሰተዳደር ባለሙያወችን ያጋጠሙ...
29/11/2024

https://p.dw.com/p/4nWxj
በዛሬው ዕለት ከጀርመን የአማርኛ ድምፅ ጋር ሰለኢትዩጵያ ሆቴሎችና ሬስቶራንቶች ዩኒፎርም አለባበስና ሰለኢትዩጵያ የሆቴል አሰተዳደር ባለሙያወችን ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን የሚገልፅ ኢንተርቢ ሊንኩን በመጫን ይስሙ።
ኢንተርቢ ተደራጊዎች ዶ/ር ሂሩት ካሳሁን የአዲስ አበባ ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊና አቶ ሉልሰገድ መሰለ የቀድሞው የኢትዩጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ፣ የአለም አቀፍ የሆቴል አሰተዳደርና የቱሪዝም ባለሙያ ።

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ ሆቴሎች ዓለም አቀፍ ደረጃን የሚያስጠብቅ የአስተናጋጆች የሥራ ልብስ ደንብ ይፋ ሆንዋል። «ደንቡ ሴቶችን ካላስፈላጊ ትንኮሳ ይከላከላል፤ የዓለም ዲፕሎማሲ ...

የባለሞያዎችን የደንብ ልብስ አለባበስና መዋቢያ በሚመለከት በአዋጅ ቁጥር 178/2016 ተፈጻሚ የሚሆን የደንብ ረቂቅ በአዲስ አበባ ፍትሕ ቢሮ በኩል ይፋ ሆኗል፡፡ ደንቡ የሆቴልና መሰል አገል...
22/11/2024

የባለሞያዎችን የደንብ ልብስ አለባበስና መዋቢያ በሚመለከት በአዋጅ ቁጥር 178/2016 ተፈጻሚ የሚሆን የደንብ ረቂቅ በአዲስ አበባ ፍትሕ ቢሮ በኩል ይፋ ሆኗል፡፡

ደንቡ የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሃገራችንን ባህልና ዕሴት በማስጠበቅ፤የባህል ወረራን የሚከላከልና የዘርፉ ባለሞያዎች ከሚደርስባቸው አካላዊና ስነ ልቦናዊ ጫናን ለማስቀረት የሚያግዝ በመሆኑ ባለሙያውም ሆነ አሰሪ አካላት በሚገባ ሊተገብሩት የሚገባ ደንብ ነው፡፡ ደንቡን ከስር ሊንኩን በመጫን በቴሌግራም ፔጃችን ላይ ያገኙታል

የኢትዩጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ጋር ውይይት አደረገ።
29/10/2024

የኢትዩጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ጋር ውይይት አደረገ።

የኢትዩጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ጋር ውይይት አደረገ። በውይይቱም የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚንስትር ክብርት ሰላማዊት ካሳ ከማህበራችን ፣ ከሆቴል ...

የኢትዩጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ጋር ውይይት አደረገ። በውይይቱም የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚንስትር ክብርት ሰላማዊት ካሳ ከማህበራችን ፣ ከሆቴል ፌዴሬሽኖች...
29/10/2024

የኢትዩጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር ከኢትዮጵያ ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ጋር ውይይት አደረገ። በውይይቱም የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚንስትር ክብርት ሰላማዊት ካሳ ከማህበራችን ፣ ከሆቴል ፌዴሬሽኖች እና ከቱሪዝም የሙያ ማህበራት ኃላፊዎች እና ተወካዮች ጋር በቅንጅት መስራት በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ተወያይተናል፡፡

በውይይታችን ማህበራችን እና የማህበራቱ ተወካዮቹ በበኩላቸው መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት ከግምት በማስገባት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱም የቱሪዝም ሳተላይት አካውንትን ማስጀመሩን በማድነቅ አሉብን ያልናቸውን ጥያቄዎች አስከትለናል። በተለይ ከደረጃ ምደባ አንጻር፣ ከእሳት አደጋ መከላከል የሚጠየቁ ፋሲሊቲዎችን በተመለከተ፣ የቀረጥ ነጻ የአንድ ጊዜ ፈቃድ ብቻ መሆን፤ በኮቪድ ምክንያት ገበያው የተቀዛቀዘው የሆቴል ኢንዱስትሪ በዳግም የደረጃው ምደባ ቁሳቁስ መቀየር ባለመቻላቸው ደረጃቸው ዝቅ ሊያደርግ ስለሚችል ከግምት ውስጥ ቢገባ የሚል እና የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ፣ በተለይ ዘርፉ ችግር ላይ በወደቀበት ሰዓት የ6 ወር እፎይታ ቢሰጠንም አመርቂ አለመሆን፣ ከውጭ የሚመጡ ባለሙያዎች የቆይታ ጊዜ እና ያበቁት የሰው ኃይል እና ዓይነት የሚለይበት አግባብ ቢፈጠር በማለት አሳስበናል።

በነዚህና ሌሎችም በተነሱ ጉዳዮች ማጠቃለያ ያደረጉት ክብርት ሚኒስትር በቀጣዩ በአጭር ፣በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ የሚፈቱ ከሰው ኃይል ስልጠና አንጻር፣ ከትብብር እና ድጋፍ እንዲሁም የሚታዩ ክፍተቶችን በጋራ የሚፈቱበትን አግባብ እና የግንኙነት ጊዜ በተመለከተ አቅጣጫ ሰጥተዋል። እኛም ጅምሩ መልካም በመሆኑ ባለሙያው የአገር ገፅታ ግንባታ ግንባር ቀደም ተሳታፊ ይሆን ዘንድ የበኩላችንን ለመወጣት ቃል ገብተን ውይይታችንን አጠናቀናል።

29/10/2024
የኢትዩጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር ከቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ በመሆን በቢሾፍቱ ከተማ ለሚገኙ ለመሰረታዊ የሆቴል አገልግሎት ሰጪ እና ለባለኮከብ ሆቴል ሰራተኞች የደንበኛ አገ...
04/10/2024

የኢትዩጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር ከቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ በመሆን በቢሾፍቱ ከተማ ለሚገኙ ለመሰረታዊ የሆቴል አገልግሎት ሰጪ እና ለባለኮከብ ሆቴል ሰራተኞች የደንበኛ አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ ትምህርት አዘል ስልጠና ተሰጥታል ፡፡
https://t.me/hoteliergroup

እንኳን  ለብርሀነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ!!!🌼🌼✝️✝️✝️✝️✝️✝️የኢትዮጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የፍቅር እንዲሆን ልባዊ ምኞታችን ነው::መልካም በዓል!!...
26/09/2024

እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ!!!🌼🌼

✝️✝️✝️✝️✝️✝️

የኢትዮጵያ ሆቴል ባለሙያዎች ማህበር በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የፍቅር እንዲሆን ልባዊ ምኞታችን ነው::

መልካም በዓል!!!

Address

Mexico
Addis Ababa
00000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Hotel Professionals Association -EHPA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share

Our Story

Ethiopian Hospitality Professionals’ Association EHPA Is The First Professional Association In Ethiopia Which Is Designed To Encourage All Hospitality Professionals (Tourism & Hotel) To Discuss Common Issues, To Share Experiences, Communicate Opportunities, Contribute To The Sector And More,