18/03/2026
የአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ
ለእድራችን አባላት በሙሉ፤
የእድራችንን መመስረትና መተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም ቀጣይ የሥራ አቅጣጫዎችን በተመለከተ በጋራ ለመምከርና ውሳኔ ለማሳለፍ የፊታችን ቅዳሜ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ተጠርቷል።
የእድር ጉዳይ የሁላችንም የጋራ መከታና መጠለያ በመሆኑ፣ እያንዳንዱ አባል ያለ ምንም ቀሪ በዚህ ጉባኤ ላይ እንዲገኝ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ቀን፦ የፊታችን ቅዳሜ (መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም)
ሰዓት፦ ከቀኑ 7:00 ሰዓት ጀምሮ
ቦታ፦ ግዮን ሆቴል (Gion Hotel)
ልዩ ማሳሰቢያ፦ በዕለቱ የአባልነት መመዝገቢያና መዋጮ ክፍያ የሚከናወን በመሆኑ፣ አባላት አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጋችሁ እንድትመጡና የአባልነት መብታችሁን እንድታረጋግጡ እናሳስባለን።
"መረዳዳት የሰላም ሕይወት መሠረት ነው!"
ከአክብሮት ጋር፤ የእድሩ ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ