16/06/2026
የባህር ዳሩ ወጣት በዎላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፊት ለፊት በስቃይ ላይ‼️
"ትላንት ሰኔ 7 ቀን ምሽት 12:00 ሰዓት አካባቢ በዎላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፊት ለፊት ባለው አስፋልት ላይ አንድ ምስኪን ወጣት መሬት ላይ ቁጭ ብሎ፣ በአካባቢው ያሉ ሰዎች ግን እንደማያዩት ሆነው እያለፉት ተመለከትኩ።
ይህ ወጣት የአእምሮ ጤናው የተስተካከለ ስላልሆነ ብቻውን እያወራና የወረቀት ብጣሾችን በእጁ እየቀነጠሰ በስ*ቃይ ላይ ነበር።
የጂንስ ሱሪ (half jeans) ለብሷል፣ ነገር ግን ጫማ የለውም! እግሩ ላይ ላስቲክ (ፔስታል) ብቻ ጠምጥሟል።
ከየት እንደመጣ ስጠይቀው "የባህር ዳር ልጅ ነኝ፤ ለትምህርት ዎላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ መጥቼ ጓደኞቼ ጥለውኝ ሄዱ" አለኝ።
ጓደኞቹ ጥለውት መሄዳቸውና ያለ እረኛ መቅረቱ በጣም የሚያሳዝን ነው።
በአሁኑ ሰዓት ወጣቱ በዩኒቨርሲቲው አካባቢ ነው የሚገኘው። ነገር ግን ምንም አይነት መረጃም ሆነ መታወቂያ በእጁ ላይ የለም።
ቤተሰቦቹ የት እንዳሉና በዚህ ሁኔታ ላይ ያለውን ልጃቸውን እያሰቡት እንደሆነ ሳስብ የልቤ ህመም ይበረታል።
እንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም! እባካችሁ ወንድማችንን እንርዳው! በፎቶው ላይ የምትመለከቱት ይህ ወጣት ምናልባት በአካልም ሆነ በፎቶ የምታውቁት ሰው ካላችሁ ወይም ቤተሰቦቹ እንዲያገኙት ይህንን መረጃ #ሼር በማድረግ እንተባበር።
በተለይ የባህር ዳር ወይም የዎላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ፣ የዚህን ወጣት ቤተሰቦች እንፈልግ‼️
ብዙ ተከታይ ያላችሁ ገጾችም ይሄንን መልዕክት በድጋሚ ብትፖስቱት የተሻለ አማራጭ ይሆናል።
ለብዙዎች እንዲዳረስ እባካችሁ ሼር አድርጉት‼️
Via- Fikre Thomas