Gamo Zone Holistic Media/የጋሞ ዞን መረጃ ማዕከል

Gamo Zone Holistic Media/የጋሞ  ዞን መረጃ ማዕከል Promoting the cultural, historical, and natural tourist attractions of the Gamo zone to the world.

በዎላይታ ዞን ሶዶ ከተማ በ8 ዓመት ሴት ልጅ ላይ አስገድዶ በመድፈር የግድያ ወንጀል የፈጸሙ ተከሳሾች በዕድመ ልክ ጽኑ እስራት ተቀጡ~~~~~~~~~~~ዳዊት ሻንቆ እና ታምራት ኦሳ የተባሉ የ...
19/06/2025

በዎላይታ ዞን ሶዶ ከተማ በ8 ዓመት ሴት ልጅ ላይ አስገድዶ በመድፈር የግድያ ወንጀል የፈጸሙ ተከሳሾች በዕድመ ልክ ጽኑ እስራት ተቀጡ
~~~~~~~~~~~
ዳዊት ሻንቆ እና ታምራት ኦሳ የተባሉ የሶዶ ከተማ ፋና ወምባ ቀበሌ ነዋሪዎች በቀን 16 /10/2016 ዓ.ም እሁድ ዕለት ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ የሶዶ ከተማ ፋና ዎምባ ቀበሌ ነዋሪ የሆነችውን የስምንት ዓመት ህጻን መሳይ አስናቀን የግብረ ሥጋ ድፍረት በደል በመፈጸም ከፍተኛ ጉዳት ካደረሱባት በኋላ በገመድ አንጠልጥለው በመግደል ከባድ የሰው ግድያ ወንጀል መፈጸማቸውን የአቃቤ ህግ የምርመራ መዝገብ ያመለክታል።

በመሆኑም የክሱን ሂደት ሲመራ የነበረው አቃቤ ህግ በኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 32(1)(ሀ) እና 539 (1)(ሀ) የተደነገገውን በመተላለፍ የተፈጸመ ከባድ የሰው ግድያ ወንጀል ነው ሲል ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።

በዚህም መነሻ በዛሬው ዕለት በቀን 12/10/2017 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት የግራ ቀኝ አስተያየት በመመርመር ፍርድ ቤቱ አቃቤ ህግ ያቀረበውን ራሷን መከላከል በማትችል የስምንት ዓመት ህፃን ላይ የተፈጸመ ወንጀል ነው ሲል ያቀረበውን የቅጣት ማክበጃ አስተያየት በመቀበል ፍርድ ቤቱ ከተሰጠው የሥልጣን እርከን አንጻር ተከሳሾቹን ያርማል፣ ሌላውን ኅብረተሰብ ከመሰል ተግባር እንዲጠነቀቅ ማስተማሪያ እና ማስጠንቀቂያ ይሆናል ብሎ በማመን ተከሳሾች በዕድመ ልክ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ በማለት በኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 32(1)(ሀ) እና 539 (1)(ሀ) እና በቅጣት አወሳሰን ቁጥር 2/2006 መሠረት ውሳኔ አስተላልፏል።

የሶዶ ከተማ አስተዳደር የሶዶ ከተማ ፖሊስ ታክቲክ ምርመራ ማስተባበሪያ ኃላፊ ኢንስፔክተር ታመነች ባሣ ወንጀሉ ተፈጽሞ ከተደበቀበት ከአራት ወር በኋላ ለከተማው ፖሊስ ጥቆማ በሟች እናት መደረሱን ገልጸው እንደገና የአካባቢውን ህዝብን በማስተባበር ምርመራ መደረጉን አውስተዋል።

ኢንስፔክተር ታመነች ባሣ አክለውም ቤተሰብ የልጆቻቸውን ውሎ በቅርበት እንዲከታተል እንዲሁም ለወንጀል ተጋላጭ ከሚያደርጉ ሁኔታዎች መጠበቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል።

ህዝቡ የወንጀል ድርጊት ከማጋለጥ አንጻር የመረጃ ምንጭ በመሆን እያገለገለ እንዲሁም እየተባበረም እንደሆነ ገልጸው ምስጋናቸውን አቅርበው ከፖሊስ ጎን እንዲቆም ጠይቀዋል።

አለሚቱ ዳሮታ የሟች ልጅ እናት ስትሆን በመጨረሻ የተሰጠው ፍርድ ተገቢ እንደሆነ እና በልጄ ሞት ያዘንኩ ቢሆንም ፍትህ በመሰጠቱ ፍርድ ቤቱን የፍትህ አካላትን እና የሶዶ ከተማ ፖሊስን አመስግነዋል።

ሰኔ 12/2017
መረጃው የዎጌታ ኤፍ ኤም 96.6

የአርባምንጭ ገበታ ለትውልድ ኮንፍረንስ ሪዞርት
19/06/2025

የአርባምንጭ ገበታ ለትውልድ ኮንፍረንስ ሪዞርት

የተፎካካሪ ፖሊቲካ ፓርቲ አመራሮች በአርባምንጭ ከተማ  በመገኘት በከተማዋ በህዝብና በመንግሥት እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው በመጎበኘት ላይ ናቸውአርባምንጭ፣ ሰኔ 12/2017...
19/06/2025

የተፎካካሪ ፖሊቲካ ፓርቲ አመራሮች በአርባምንጭ ከተማ በመገኘት በከተማዋ በህዝብና በመንግሥት እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው በመጎበኘት ላይ ናቸው

አርባምንጭ፣ ሰኔ 12/2017 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን) በሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የተለያዩ የተፎካካሪ ፖሊቲካ ፓርቲ አመራሮች ዛሬ በአርባምንጭ ከተማ ተገኝተው በህዝብ ተሳትፎና በመንግሥት የሚሠሩ ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው እየጎበኙ ናቸው።

አመራሮቹ ከሰዓት በፊት ከጎበኟቸው የልማት ሥራዎች መካከል በገበታ ለትውልድ ፕሮግራም እየተገነባ ያለው አርባምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርትና በሀገሪቱ ብቸኛው የአርባምንጭ አዞ ራንች ይገኙበታል።

እንግዶቹ ልማቶቹን በጎበኙበት ወቅት የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ፣ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶ/ር መስፍን መንዛ እና ሌሎች የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ የጋሞ ዞንና የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግስትና የብልጽግና ፓርቲ የሥራ ኃላፊዎች ልማቶቹ የሚኖራቸውን ፋይዳ ገልጸውላቸዋል።

በተጨማሪም የየፕሮጀክቶቹ ሥራ አስኪያጆች እና አስተባባሪ አካላቱ ፕሮጀክቶቹን በተመከተ ለጎብኝዎች ሰፋ ያለ ገለጻ አድርገዋል።

እንግዶቹ ከምሳ ዕረፍት በኋላም በከተማው በህዝብ ተሳትፎ ግንባታው እየተፋጠነ ያለው አለምአቀፍ ስታዲየምን ጨምሮ ሌሎች ፕሮጀክቶችን እንደሚጎበኙ ይጠበቃል።

የእንሰሳት መኖ ሽያጭ ~~~~~~~~በጋሞ ልማት ማህበር የጉጌ እንስሳት ዕርባታ ያለማውን የተለያዩ የእንስሳት መኖውን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመሸጥ ይፈልጋል:: በመሆኑም ለመግዛት የሚፈልግ አካል በ...
19/06/2025

የእንሰሳት መኖ ሽያጭ
~~~~~~~~
በጋሞ ልማት ማህበር የጉጌ እንስሳት ዕርባታ ያለማውን የተለያዩ የእንስሳት መኖውን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመሸጥ ይፈልጋል:: በመሆኑም ለመግዛት የሚፈልግ አካል በአካል ማሳ ቀርበው በድርድር የሚበቃውን መግዛት እንደሚችል እንገልፃለን::

አደራሻ: ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ኮሌጅ 100 ሜትር ወደ አየር ማረፊያ በመጓዝ ማግኘት ይችላሉ:: ለተጨማሪ መረጃ +251913749985 ስልክ ላይ ይደውሉ

19/06/2025

በጋሞ ዞን በህብረተሰቡ ተሳትፎ ከተሰሩ ሥራዎች መካከል አንዱ የሠላምበር ኮርደር ልማት አካል የሆነው የመንገድ መብራት ዝርጋታ ነው:: ይህም የከተማውን ውበትና ገፅታ በእጅጉ ጨምሯል:: የህዝብና የመንግሥት መተባበር አሁን የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ ያጠናክራል!

ሁለንተናዊ ዕድገት ለጋራ ተጠቃሚነት!
ሰኔ 12/2017 ዓ/ም
Degu Desalegn Damota

የጋሞ  አባቶች ጠብቀው ለትውልድ ያስተላለፉትን ባህላዊ መሰብሰብያ አደባባዮች (ዱቡሻ ቦታዎች) ጥበቃና እንክብካቤ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የጋሞ ዞን አስተዳደር አሳሰበ።~~~~~~~~~~~~የጋሞ ...
19/06/2025

የጋሞ አባቶች ጠብቀው ለትውልድ ያስተላለፉትን ባህላዊ መሰብሰብያ አደባባዮች (ዱቡሻ ቦታዎች) ጥበቃና እንክብካቤ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የጋሞ ዞን አስተዳደር አሳሰበ።
~~~~~~~~~~~~
የጋሞ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ከአንጋፋው አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመቀናጀት የዱቡሻ ቦታዎች ልየታና ልኬት ስራ በጨንቻ ከተማና ጨንቻ ዙሪያ ወረዳ ጀምሯል፡፡

የጋሞ ዱቡሻ ዘመን ተሻጋሪ ለሀገር ልማትና ለሀገር ሰላም ግንባታ ቀጣይነቱን እንዲያረጋግጥ ለማስቻል የዱቡሻ ቦታዎች ልየታና ልኬት (Mapping) ሥራ አስፈላጊ መሆኑን የጋሞ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ አቶ ሞናዬ ሞሶሌ የገለጹ ሲሆን በቀጣይ በሁሉም በዞናችን ባሉት ወረዳዎች እና ከተሞች ሥራዎች ይቀጥላል ብለዋል።

በጋሞ ዞን ጨንቻ ከተማ የጦሎላ ሴቶች ወተት አምራች መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር ከ26.5 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራቱን ገለፀ ~~~~~~~~~~~~~~ጦሎላ የሴቶች ወተት አምራች መሰረታ...
19/06/2025

በጋሞ ዞን ጨንቻ ከተማ የጦሎላ ሴቶች ወተት አምራች መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር ከ26.5 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራቱን ገለፀ
~~~~~~~~~~~~~~
ጦሎላ የሴቶች ወተት አምራች መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ጨንቻ ከተማ ይገኛል:: ማህበሩ የተመሰረተው በ1997 ዓ.ም በ105 ሴቶች እና በአምስት ወንዶች ነው፡፡

በአሁኑ ወቅት 196 ሴት እና አምስት ወንድ በድምሩ 201 አባላትን አቅፎ እየሰራ ይገኛል፡፡ ኅ/ሥ/ማህበሩ ከ26.5 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ማፍራት የቻለ ሲሆን ለ24 ሰዎችም ቋሚ እና ጊዜያዊ የስራ እድል መፍጠር ችሏል፡፡

ማህበሩ ወተት እና የወተት ተዋፅኦዎችን በስፋት እና በዘመናዊ መልኩ በማምረት እስከ አርባ ምንጭ ከተማ ድረስ ካሉ ድርጅቶች ጋር የንግድ ትስስር መፍጠር ችሏል፡፡

ሲመሰረት ነገሮች አልጋ ባልጋ እንዳልነበሩ የሚናገሩት የማህበሩ ሰብሳቢ ወ/ሮ ፀሃይ ቡሳ ጥሩ የወተት ምርት የሚሰጡ ከብቶችን ከማግኘት ጀምሮ የተመረተው ወተት ባካባቢው ላይ ገበያ የማግኘት ችግር እንደነበር ነግረውናል፡፡

በዚህም የገጠማቸውን የገንዘብ ችግር ለማካካስ ጥጥ እየፈተሉ ጋቢ በመስራት እና ሽሮ እና በርበሬ በማስፈጨት እና በመሸጥ ማህበራቸውን ከኪሳራ ለመታደግ መቻላቸውን ይናገራሉ፡፡

በተለይም በወቅቱም ከአካባቢው ባህል ጋር ተያይዞ ትኩስ ወተት ገበያ አውጥቶ ለመሸጥ ፈተና ሆኖባቸው እንደነበር የሚናገሩት ሰብሳቢዋ ቀስ በቀስ የማሳመን ስራ በመስራት ገበያ ውስጥ መግባት እንደቻሉ ነግረውናል ሲል የዘገበው የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን ነው፡፡

በጌዴኦ ዞን ለቡሌ ከተማ ዕድገት የበኩላቸውን እንደሚወጡ የከተማው  ነዋሪዎች ገለፁ~~~~~~~~~~~~~~~በጌዴኦ ዞን የቡሌ ከተማ አስተዳደር በፈርጅ 3 የምስረታ ፕሮግራም ተካሂዷል::  በ1...
19/06/2025

በጌዴኦ ዞን ለቡሌ ከተማ ዕድገት የበኩላቸውን እንደሚወጡ የከተማው ነዋሪዎች ገለፁ
~~~~~~~~~~~~~~~
በጌዴኦ ዞን የቡሌ ከተማ አስተዳደር በፈርጅ 3 የምስረታ ፕሮግራም ተካሂዷል:: በ1882 ዓ.ም እንደተቆረቆረች የሚነገርላት የቡሌ ከተማ በደጋ ድንች፣ በአኘል ምርት፣ በቅጠል ሽንኩርት፣ በአተር፣ በባቄላ፣ በገብስ፣ በእንስሳት ሀብትና በሌሎች ሰብሎች የሚታወቅ ሲሆን በዞኑ ከሚገኙ ወረዳዎች ትርፍ አምራች ወረዳ በመባል ትታወቃለች::

አካባቢው ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ፣ ታርካዊ የመስህብ መዳረሻ፣ የበርካታ ፀጋዎች ያሉበት በመሆኑ እነዚህን በአግባቡ በመጠቀም የኢኮኖሚ ማዕከል ማድረግ ያስፈልጋል ተብሏል።

ለጌዴኦ ቴሌቭዥን አስተያየታቸውን የገለጹት ነዋሪዎቹ ከተማው የከተማ አስተዳደርነት ዕውቅና ማግኘቷ እንዳስደሰታቸው በመግለፅ ለከተማው ዕድገት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ የበኩላቸውን እንደሚወጡ አስረድተዋል ሲል የዘገበው ጌዴኦ ቴሌቭዥን ነው::

የሰሊጥ ምርት በባስኬቶ ዞን~~~~~~~በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ አንግላ ክላስተር በኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ እየለማ ያለ የሰሊጥ ምርት ሲሆን በዞኑ ከሚለማው ሰሊጥ 720 ሄ/ር መሬት...
19/06/2025

የሰሊጥ ምርት በባስኬቶ ዞን
~~~~~~~
በባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ አንግላ ክላስተር በኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ እየለማ ያለ የሰሊጥ ምርት ሲሆን በዞኑ ከሚለማው ሰሊጥ 720 ሄ/ር መሬት በኩታ ገጠም አስተራረስ ዘዴ እየለማ መሆኑ ተመላክቷል።

አሊያንስ ኮሌጅ የ250,000 ሺ ብር ድጋፍ አደረገ~~~~~~~~~~~~~ በአርባምንጭ ዮኒቨርስቲ ሙሁራን ተቋቁሞ ለከተማችን የሰለጠነ የሰው ሀይል  እያፈራ ያለው ኮሌጃችን አሊያንስ   በከተማ...
19/06/2025

አሊያንስ ኮሌጅ የ250,000 ሺ ብር ድጋፍ አደረገ
~~~~~~~~~~~~~
በአርባምንጭ ዮኒቨርስቲ ሙሁራን ተቋቁሞ ለከተማችን የሰለጠነ የሰው ሀይል እያፈራ ያለው ኮሌጃችን አሊያንስ በከተማችን የእድገት ስራዎችም የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል።

በዚህም መሰረት በከተማችን እየተገነባ ለሚገኘው የአርባምንጭ አለም ዓቀፍ ስቴዲየም ግንባታ ድጋፍ እንዲሆን የ 250,000 ሺ (ሁለት_መቶ_ሀምሳ_ሺ ብር) ድጋፍ ያደረግን መሆኑን እየገለፅን ለወደፊትም የከተማችን ልማት ከፍ ብሎ እንድታይ በተጀመሩ የእድገት ለውጦች አጋርነታችንን የምናስቀጥል መሆኑን እንገልፃለን። አሊያንስ ኮሌጅ የእውቀት ድግስ !

የጋሞ አትክልት እና ፍራፍሬ ዩኒየን ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማፍራቱ ገለፀ ~~~~~~~~~~~~~ዩኒየኑ በ35 ሺህ ብር ካፒታል ስድስት መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበራትን ይዞ በ1997...
18/06/2025

የጋሞ አትክልት እና ፍራፍሬ ዩኒየን ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማፍራቱ ገለፀ
~~~~~~~~~~~~~
ዩኒየኑ በ35 ሺህ ብር ካፒታል ስድስት መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማህበራትን ይዞ በ1997 ዓ.ም ተመሰረተ፡፡ በአሁኑ ወቅት ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል ማፍራት ችሏል፡፡

በአሁኑ ወቅት 30 ማህበራትን አቅፎ እየሰራ የሚገኘው ዩኒየኑ በርካታ ውጤታማ ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ ሲሆን ከነዚህም ስራዎች መካከል የእንስሳት መኖ በዘመናዊ መልክ ያቀነባብራል፣ አትክልት እና ፍራፍሬዎች ያመርታል ያከፋፍላል እንዲሁም የተለያዩ የግርና ግብዓቶችን ለአርሶ አደሮች የማከፋፈል ስራ እየሰራ እንደሚገኝ የነገሩን የጋሞ አትክልት እና ፍራፍሬ ዩኒየን ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሲሳይ ቦጋለ ናቸው፡፡

ዩኒየኑ ሙዝ ወደውጭ ሀገር ኤክስፖረት ማድረግ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም ከትራንስፖርት ወጪ ጋር በተያያዘ መቀጠል ሳይችሉ መቅረታቸውን የነገሩን የቦርድ ሰብሳቢው በቀጣይ ሙዝ በማቀነባበር ለገበያ ለማቅረብ እየሰሩ መሆኑን ነግረውናል ሲል የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን ነው::

የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትጋት እየሰራ መሆኑን የመሌ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት አስታወቀ።በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት የመሌ ማዘጋጃ...
18/06/2025

የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትጋት እየሰራ መሆኑን የመሌ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት አስታወቀ።

በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት የመሌ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ከውስጥ በሚያገኘው ገቢ እና በማህበረሰቡ ተሳትፎ የገንዘብ ድጋፍ 2 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ የመጀመሪያ ዙር የመንገድ ከፈታ ጥርጊያ እና የጠጠር ንጣፍ ሥራ ተጠናቆ ለአገልግሎት ይበቃ ዘንድ ርክክብ ተከናውኗል።

በርክክብ ስነስርዓቱ ወቅት አቶ ዘለቀ ዛፋ የመሌ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ሥራአስኪያጅ ባስተላለፉት መልዕክት የህብረተሰቡን የልማት ጥያቄ ለመመለስ በትጋት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤቱ በክልሉ መንግሥት እውቅና ከተሰጠበት ጀምሮ በአጭር ጊዜ በርካታ መሠረተ ልማቶችን በማከናወን ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ዘለቀ ይህ የ 2.7 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ የመጀመሪያ ዙር የመንገድ ከፈታ ጥርጊያ እና የጠጠር ንጣፍ ሥራ ለአብነት ተጠቃሽ መሆኑን ገልፀዋል።

የውስጥ ለውስጥ የመጀመሪያ ዙር የመንገድ ከፈታ ጥርጊያ እና የጠጠር ንጣፍ ሥራው 5.1 ሚሊየን ብር የገንዘብ ወጪ የፈጀ መሆኑንም ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል።

የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት የወረዳው ፋይናንስና ፕላን ጽ/ቤት ባለሙያዎች በርክክብ ሥነሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል ሲል የዘገበው የአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ነው::

Address

Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Holistic Media/የጋሞ ዞን መረጃ ማዕከል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gamo Zone Holistic Media/የጋሞ ዞን መረጃ ማዕከል:

Share