Gamo Zone Holistic Media/የጋሞ ዞን መረጃ ማዕከል

Gamo Zone Holistic Media/የጋሞ  ዞን መረጃ ማዕከል Promoting the cultural, historical, and natural tourist attractions of the Gamo zone to the world.

10/07/2025

"አመራሩ የራሱን ድርሻ ከምንም ነፃ ሆኖ መወጣት አለበት፤ የአመራር የሐሳብና የተግባር አንድነት እንድኖር ከሰራን የክልላችን አንድነት እውን የማይሆንበት ምንም ምክንያት የለውም።"

ወ/ሮ ልሳነወርቅ ካሳዬ
የአርባምንጭ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ

09/07/2025

የገጠር ኮሪደር ስንል ፍላጎታችን ሶላር ያለው፣ ሽንት ቤት ያለው፣ ባዮጋዝ ያለው፣ የሰው ማደሪያና የከብት ማደሪያ የተለየ ቤት ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

የጋሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ  የጨንቻ  ሆስፒታል ደረጃ  ማሻሻያ ስራዎች ያለበትን ሂደት ጎብኙ~~~~~~~~~~~የሆስፒታሎች ደረጃ ማሻሻል የታካሚዎችን ደህንነት እና የህክ...
08/07/2025

የጋሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ የጨንቻ ሆስፒታል ደረጃ ማሻሻያ ስራዎች ያለበትን ሂደት ጎብኙ
~~~~~~~~~~~
የሆስፒታሎች ደረጃ ማሻሻል የታካሚዎችን ደህንነት እና የህክምና ጥራት ከፍ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ፣ የጤና ባለሙያዎችን አቅም በማጎልበት አጠቃላይ የጤና አጠባበቅ ስርዓቱን እንደሚያጠናክርም ዋና አስተዳዳሪው በምልከታው ወቅት ጠቁመዋል።

የጨንቻ የመጀመሪያ ሆስፓታል አንጋፋ ሆሲፒታል መሆኑን የጠቁሙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ባለፉት 90 ቀናት አቅጣጫ ተቀምጦ ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው በክልሉ ጤና ቢሮ አማካኝነት በጥቂት ቀናት ውስጥ የአጠቃላይ ሆስፒታል እውቅናን እንደሚያገኝም ገልፀዋል።

የጨንቻ ሆስፒታል ደረጃ በማሻሻል እረገድ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድርን ጨምሮ ሁሉም ህብረተሰብ ከሀሳብ እስከ ገንዘብ ድጋፍ ያደረገበት የህዝቡ አንድነት የተጠናከረበት እንደሆነም ተናግረዋል።

ሆስፓታሎች ደረጃቸውን ሲያሻሽሉ፣ የታካሚዎችን ደህንነት እና እንክብካቤ ለማረጋገጥ የተሻሉ ስርዓቶችን እና ሂደቶችን ይዘረጋልም ብለዋል።

ግብር ለአንድ ሀገር እድገት፣ ልማትና ብልጽግና ጉልህ ሚና አለው ዶ/ር መስፍን መንዛ የአርባምንጭ ከተማ ከንቲባበአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የ 2017 በጀት ዓመት የግብር መክፈያ እና የ20...
08/07/2025

ግብር ለአንድ ሀገር እድገት፣ ልማትና ብልጽግና ጉልህ ሚና አለው ዶ/ር መስፍን መንዛ የአርባምንጭ ከተማ ከንቲባ

በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር የ 2017 በጀት ዓመት የግብር መክፈያ እና የ2018 የንግድ ፈቃድ እድሳት በይፋ ተጀመረ

አርባምንጭ፡ሐምሌ 1/2017 ዓ/ም (አርባምንጭ ከተማ መ/ኮሚዩኒኬሽን)

በአርባምንጭ ከተማ የ2017 የደረጃ"ሐ" ግብር አሰባሰብ ንቅናቄ የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶ/ር መስፍን መንዛን ጨምሮ የከተማው ብልጽግና ፓርቲ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ማዶ መንገሻ፣ የከተማ አመራሮችና የጋሞ አባቶች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል።

የአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዶ/ር መስፍን መንዛ ግብር ለአንድ ሀገር እድገት፣ ልማትና ብልጽግና ጉልህ ሚና እንዳለው ተናግረው ይህንን ለማረጋገጥ ህብረተሰቡ ግብሩን በአግባቡ ሊከፍል ይገባል ብለዋል።

በከተማው ከ14 ሺ በላይ የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች መኖራቸዉ ገልፀው በከተማው ያሉ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን በተገቢው መንገድ ለመመለስ ገቢ አሰባሰብ በአግባቡ በዘመናዊ በኤሌክትሮኒክስ መንገድ ሳይጨናነቅ በተዘጋጁ ማዕከላት በመምጣት ግብሩን በተቀመጠው ጊዜ እንዲከፍል ጥሪ አቅርበዋል።

በከተማው ትላልቅ ፕሮጀክቶችና በርካታ መሠረተ ልማት እየተሰሩ እንደሚገኙ የጠቀሱት ከንቲባው የተጀመሩ የትምህርት፣ የጤና፣ የመንገድ እና ሌሎች መሰረተ ልማት ግንባታ ስራዎች ውጤታማነታቸው እንዲረጋገጥና በተባለለት ጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ገቢን አሟጦ መሰብሰብ እንዳለበትም አስረድተዋል።

ህብረተሰቡም የከተማውን ልማት ማፋጠን የሚቻለው ግብር በአግባቡኢ ሲከፈል እንደሆነ ተናግረው የተጀመረው ልማት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ግብር ከፋዮች ግብርን በታማኝነት መክፈል እንዳለበት ተገልጿል።

የደረጃ "ሐ" የግብር አከፋፈል እና የንግድ ስራ ፈቃድ እድሳት ስራ በዘርፉ ባለሙያዎች እና የአመራሩ የቅርብ ክትትል እና ቅንጅት በጥሩ ሁኔታ ከሐምሌ 1--10/2017 ዓ/ም እንደሚቀጥል አመልክተዋል።

የደረጃ "ሐ" ግብር ከፋዩ ህብረተሰብ መደበኛ ግብር፣ ማዘጋጃ ቤታዊና አከራይ ተከራይ ግብር በመክፈልና የ2018 ንግድ ስራ ፈቃድ ማደስ እንደሚገባው ተጠቁሟል።

የንግዱ ማህበረሰብ ከዛሬ ሐምሌ 1/2017 ዓ.ም 12:00 ሰዓት ጀምሮ በተቀመጠው ጊዜ ገደብ ግብሩን ከፍሎ እንዲያጠናቅቅ የአንድ መስኮት አገልግሎት መስጫ ማዕከላት በይፋ ስራ ተጀምሯል።

የአርባ ምንጭ ትምህርት ኮሌጅ ‘’ከሰራን እናድጋለን’’ ከተሰኘ የሕንጻ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ጋር በ84 ሚልየን ብር የተማሪዎች ማደሪያ ለማስገንባት የውል ስምምነት ተፈራረመ~~~~~~~~~~~~...
08/07/2025

የአርባ ምንጭ ትምህርት ኮሌጅ ‘’ከሰራን እናድጋለን’’ ከተሰኘ የሕንጻ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ጋር በ84 ሚልየን ብር የተማሪዎች ማደሪያ ለማስገንባት የውል ስምምነት ተፈራረመ
~~~~~~~~~~~~~
የአርባ ምንጭ ትምህርት ኮሌጅ ‘’ከሰራን እናድጋለን’’ ከተሰኘ የሕንጻ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ጋር በ84 ሚልየን ብር በጀት የሚገነባ የተማሪዎች ማደሪያ ክፍል ግንባታ የውል ስምምነት ሰኔ 30/2017 ዓ/ም ተፈራርሟል፡፡ በዕለቱም የግንባታ ሳይት ርክክብ ተካሂዷል፡፡

የግንባታ ሂደቱ ለሦስት መቶ ስልሳ ቀናት የሚቆይ ሲሆን ከአራት መቶ በላይ ተማሪዎችን ማስተናገድ የሚችል የተማሪዎች ማደሪያ መሆኑን በውል ስምምነቱ ላይ ተካቷል፡፡

በፕሮግራሙ ላይም የኮሌጁ ማኔጅመንት አባላትን ጨምሮ የክልል ኮንስትራክሽንና ዲዛይን መሀንዲሶች ተገኝተዋል፡፡

የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ከ22.5 ሚሊየን ብር በላይ እየተገነባ  የሚገኘ የኤልጎ ጤና ጣቢያ ህንፃ ግንባታ የመስክ ምልከታ ተደረገ።~~~~~~~~~~~~~በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዘይሴ ኤልጎ ቀበሌ በወረዳው መንግሥት...
07/07/2025

ከ22.5 ሚሊየን ብር በላይ እየተገነባ የሚገኘ የኤልጎ ጤና ጣቢያ ህንፃ ግንባታ የመስክ ምልከታ ተደረገ።
~~~~~~~~~~~~~
በአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዘይሴ ኤልጎ ቀበሌ በወረዳው መንግሥት የገንዘብ ወጪ ከ22.5 ብር ተገንብቶ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኘው የኤጎ ጤና ጣቢያ ህንፃ ግንባታ ነባራዊ ገፅታ የመስክ ምልከታ ተደረገ።

የተጀመሩ የመሠረተ ልማቶች በአግባቡ ተጠናቀው ለህብረተሰቡ አገልግሎት ይሰጣሉ ያሉት አቶ አለማየሁ ዘይቴ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ በዚህም በህብረተሰቡ ዘንድ በጥያቄ ስነሳ የነበረው የጤና ጣቢያ ህንፃ ግንባታ በአጭር ጊዜ በመገንባት በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ይበቃ ዘንድ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ተናግረዋል።

በመስክ ምልከታው ላይ አቶ ጌታሁን ሸጋ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ምክትል አስተዳዳር እና ከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ ጨምሮ የወረዳው የመንግሥትና ፓርቲ ሥራ ኃላፊዎች የቀበሌው አመራሮች ተገኝተዋል።

ሰኔ፣ 30/2017 ዓ.ም
(የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

በጋሞ ልማት ማህበር ቦረዳ ቅርንጫፍ ሞታ መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ሥራና ተግባር ትምህርት ዘርፍ ተጓዳኝ ክበብ ሁሉንም የት/ቤት መምህራንና ተማሪዎችን በማሳተፍ በግቢ ውስጥ የሚገኙ የእርሻ ሥራ...
07/07/2025

በጋሞ ልማት ማህበር ቦረዳ ቅርንጫፍ ሞታ መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት ሥራና ተግባር ትምህርት ዘርፍ ተጓዳኝ ክበብ ሁሉንም የት/ቤት መምህራንና ተማሪዎችን በማሳተፍ በግቢ ውስጥ የሚገኙ የእርሻ ሥራ ውጤት የሆኑ የተለያዩ ችግኞችን የመንከባከብ ሥራዎች እንድሁም የጽዳት ዘመቻ አካሂዷል።

ቅድማያ ለጋራ ልማት!
ሰኔ 30/2017 ዓ.ም

"በራስ አቅም ወደ ብልፅግና ለመሸጋገር በሚደረግ ሂደት ግብርን በወቅቱ መክፈል የማይተካ ሚና አለው" የክልሉ ገቢዎች ቢሮ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2017 የግብር ዘመን ማስጀመሪ...
07/07/2025

"በራስ አቅም ወደ ብልፅግና ለመሸጋገር በሚደረግ ሂደት ግብርን በወቅቱ መክፈል የማይተካ ሚና አለው" የክልሉ ገቢዎች ቢሮ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2017 የግብር ዘመን ማስጀመሪያ ቀንን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል

የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ መግለጫውን በሰጡበት ወቅት እንደገለፁት ሀገራችን ኢትዮጵያ በራስ አቅም ወደ ብልፅግና ለመሸጋገር በሚደረገው ሂደት ግብርን በወቅቱ መሠብሰብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው ብለዋል።

በክልሉ ከ125 ሺህ በላይ የደረጃ " ሀ "፣"ለ" እና "ሐ" ግብር ከፋዮች ይገኛሉ ያሉት የቢሮው ኃላፊዋ በግብር ህጉ በተቀመጠው መሰረት እንደ ግብር ከፋይነት ደረጃቸው በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ግብራቸውን ሊከፍሉ እንደሚገባም ተናግረዋል።

በክልሉ 115 ሺህ የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች የሚገኙ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 83 ሺህ የሚሆኑት በቴሌ ብር እንዲከፍሉ ለማድረግ ዝግጅት መጠናቀቁንም ወ/ሮ አለምነሽ አመላክተዋል።

የ2017 ግብር ዘመን መክፈያ ወቅት ሐምሌ 01/2017 ዓ.ም ይጀምራል ያሉት የቢሮው ኃላፊ ከደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች በ10 ቀናት ወስጥ 1 ቢሊዮን ብር ለመሠብሰብ መታቀዱንም በጋዜጣዊ መግለጫዉ ጠቁመዋል።

ለግብር ዘመኑ ከመደበኛ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት በተጨማሪ 230 ጊዜያዊ የታክስ መክፈያ ማዕከላት መደራጀታቸውን የጠቀሱት የቢሮው ኃላፊዋ ይህም የንግዱ ማህበረሰብ ጊዜውንና ጉልበቱን በመቆጠብ ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው ብለዋል።

የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች የተዘጋጁለትን ምቹ ሁኔታዎች በመጠቀም ሳይዘናጋ ከሐምሌ 01/2017 ዓ.ም ከመጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ ወደተዘጋጁት የመክፈያ ማዕከላት በመሄድ እንዲከፍሉም ጥሪ አስተላልፈዋል።

በየደረጃው የሚገኙ የገቢ ተቋማትም የግብር አከፋፈል ስርዓቱን ለግብር ከፋዮች ምቹ፣ ቀልጣፋና ተደራሽ እንዲሆን በርካታ ስራዎች መከናወናቸውንም ወ/ሮ አለምነሽ አመላክተዋል።

የደረጃ ሀ እና ለ ግብር ከፋዮችም ሳይዘናጉ ዓመታዊ ግብራቸውን በወቅቱ በመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን ሊወጡ እንደሚገባም የቢሮው ኃላፊዋ አሳስበዋል።

06/07/2025

የጨንቻ ከተማ ትንሳኤ

የመኪና አደጋ የደረሰባቸው የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከጉዳታቸው አገግመው ለፈተናው ዝግጁ መሆናቸውን የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ አስታወቀአርባምንጭ፥ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም (ጋሞ ዞን ...
06/07/2025

የመኪና አደጋ የደረሰባቸው የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከጉዳታቸው አገግመው ለፈተናው ዝግጁ መሆናቸውን የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ አስታወቀ

አርባምንጭ፥ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን)

በጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር አዲሱ አዳሙ የተመራ ልዑክ አደጋ የደረሰባቸው ተማሪዎችን በአርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ ዋናው ግቢ በመገኘት ጎብኝተዋል።

የጋሞ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር አዲሱ አዳሙ በጉብኝቱ ወቅት እንደተናገሩት ለሀገር አቀፍ 12 ክፍል ፈተና ከቦረዳ ወደ አርባ ምንጭ ሲጓዙ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች ከጉዳታቸው አገግመው በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙና ሁሉም ለፈተናው ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች ከነገ በስቲያ ለሚሰጠው 12 ክፍል ፈተና በአካልም ሆነ በስነ ልቦና ራሳቸውን ለማዘጋጀት ጥረት እያደረጉ ስለመሆኑ በጉብኝቱ መታዘባቸውን ዶ/ር አዲሱ ተናግረዋል።

አክለውም ከአደጋው ከደረሰበት ቀን ጀምሮ ተማሪዎችን በማጽናናት፣ ክትትል በማድረግና በተለያዩ ነገሮች የተባበሩ አካላትን ዶ/ር አዲሱ አመስግነዋል።

የአርባ ምንጭ ዩንቨርስቲ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተርና የዋናው ግቢ ዲን የሆኑት ዶ/ር ሙሉነህ ለማ በበኩላቸው ጉዳት የደረሰባቸውን ተማሪዎች ከአቀባበል ጀምሮ በግቢው ልዩ እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑን አስረድተዋል።

በአደጋው የከፋ አደጋ በተማሪዎች ላይ እንዳልደረሰ የተናገሩት ዶ/ር ሙሉነህ ቀለል ያሉ ጉዳቶችን በግቢው በሚገኝ ክሊኒክ ህክምና እየተሰጣቸው እንዳለና ከአቅማቸው በላይ የሆኑ ጉዳቶችን በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ክትትል እያደረጉ እንደሆነና በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኑ ገልፀዋል።

የጋሞ ዞን ፖሊስ የትራፊክ አደጋ መከላከልና ቁጥጥር ዲቪዠን ኃላፊ ም/ኩማንደር እያሱ ፓርደ በቀን 28/2017 ዓ.ም በብርብር ከተማ በተለምዶ ትልቁ ዳገት በሚባለው ስፍራ ከቦረዳ ወረዳ ተማሪዎችን ጭና ወደ አርባ ምንጭ ከሚመጣ ባስ ጋር በተቃራኒው ከአርባ ምንጭ ወደ ወላይታ ተሳፋሪዎችን ይዞ ሲጓዝ ከነበረ የህዝብ ማመላለሻ ጋር በማጋጨት አደጋው መድረሱን አስታውሰዋል።

የአደጋው መንስኤ የአሽከርካሪዎች ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር መሆኑን ም/ኩማንደር ጠቅሰው በአደጋው አንድ ተማሪ ከባድ ጉዳት ሲያስተናግድ ስድስት ተማሪዎች ላይ ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ግብረ ሃይል ተቋቁሞ በተደረገው ጥረት ሁሉም በሚባል ደረጃ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙም ገልፀዋል።

በአደጋው የተጎዱ ተማሪዎችም ከደረሰባቸው ጉዳት በማገገም ለፈተናው እየተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ መልቀቂያ ፈተና የፊታችን ማክሰኞ ሀምሌ 01 መሰጠት ይጀምራል።

06/07/2025

የጨንቻ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ወደ አጠቃላይ ሆስፒታል

የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ሀምሌ 1 ለሚጀመረው የታክስ ንቅናቄና የግብር አሰባሰብ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ማጠናቀቁን አስታወቀ።~~~~~~~~~የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ቶማስ ቶቤ ...
06/07/2025

የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ሀምሌ 1 ለሚጀመረው የታክስ ንቅናቄና የግብር አሰባሰብ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ማጠናቀቁን አስታወቀ።
~~~~~~~~~
የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ቶማስ ቶቤ በዞኑ 18 ሺህ 580 የደረጃ 'ሐ' ግብር ከፋዮች መኖራቸውንና ከደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች 8 ሺ 682 የሚሆኑት በቴሌ ብር ግብራቸውን የሚከፍሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም ከሀምሌ አንድ ጀምሮ ባለው ጊዜ የ2017 የግብር ዘመን የግብር አሰባሰብ ሁሉም የደረጃ " ሐ" ግብር ከፋዮች በአንድ ሳምንት ውስጥ ግብራቸውን እንዲከፍሉና የንግድ ፈቃድ እድሳት በአንድ ማእከል አገልግሎት በማከናወን ወደ መደበኛ ስራቸው መመለስ እንዲችሉ በሁሉም መዋቅሮች የቅድመ ዝግጅት ሥራዉ መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡

ለግብር ከፋዮችም በየማዕከላቱ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጥ ከኢንቴርኔት ፍጥነት ማነስና መቆራረጥ ጋር የሚገጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ የኢትዮ-ቴሌኮሚኒኬሽን በቅርበት ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑና በቴሌ ብር ከማስከፈል ጋር ተያይዞ የሚታየውን ተግዳሮት ለመቅረፍ ከቴሌ ኤጀንቶች ጋር የግንዛቤ ስራዎችን ከወዲሁ በመስራት የ2017 የገቢ አሰባሰብና የ2018 የንግድ ፈቃድ ምዝገባና እድሳት ስራ በአግባቡ ለመስራት መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።

ስለሆነም የንግዱ ማህበረሰብ ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ በአቅራቢያዉ በጊዜያዊነት አገልግሎት ለመስጠት በተደራጁ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት እየቀረበ ያለምንም መጉላላት፣ ተጨማሪ ወጪ ባለማዉጣት የ2017 በጀት ዓመት መደበኛ ግብር/ታክስ፣ የማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ግብር እንዲከፍሉና እና የ2018 በጀት ዓመት የንግድ ሥራ ፈቃድ ዕድሳት እንድያደርጉ የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ቶማስ ቶቤ ጥሪ አሰተላልፈዋል፡፡

ሰኔ 29/10/2017
(የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ)

Address

Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Zone Holistic Media/የጋሞ ዞን መረጃ ማዕከል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gamo Zone Holistic Media/የጋሞ ዞን መረጃ ማዕከል:

Share