ሙሐመድTour&trave

ሙሐመድTour&trave By visiting �web band entertainment without it simply

09/10/2025

የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው እንዲኖሩ ለመቀበል ዝግጁ ነን

አዲስ አበባ፤ መስከረም 29/2018(ኢዜአ)፦ ከወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሸተ ደምለው እና የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በሰጡት ማብራሪያ፤ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱና ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አሸተ ከዞኑ የተፈናቀሉና ያልተመለሱ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ እንደሚቀበሏቸው ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በወልቃይት ጠገዴ የሚኖሩ በርካታ የትግራይ ተወላጆች ሰላማዊ ህይወታቸውን እየመሩ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ የአማራና የትግራይ ህዝብ ለዘመናት አብረው የኖሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የሰሜኑ ጦርነት በተከሰተበት ወቅት ብዙዎች በኖሩበት አካባቢ እየኖሩ መሆኑን አስታውሰው፤ በወቅቱ ተደናግጠው ከሄዱት መካከል ደግሞ ወደ ዞኑ ተመልሰው ሰላማዊ ህይወት መምራት የጀመሩ መኖራቸውን ተናግረዋል።

ምክትል ዋና አስተዳዳሪው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በበኩላቸው እንደገለጹት ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ አካባቢያቸው መመለስ አለባቸው።

በአካባቢው ሰላም ለመፍጠር አንድን ማህበረሰብ አፈናቅለህ አንዱን ማኖር የሚቻል አይመስለኝም ብለዋል።

ምክትል ዋና አስተዳዳሪው፤ የተፈናቃዮች ጉዳይ በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝ በሁሉም በኩል ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል።

መንግስት ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለማድረግ በተከታታይ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውንና ጥረቶች ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል።

#ኢዜአ

09/10/2025

ከምግብ በኋላ ፈፅሞ የማይመከሩ ነገሮች

1. #ሻይ አይጠጡ
ሻይ በሰውነታችን ከፍተኛ መጠን ያለው አሲድ እንዳይፈጠር ያደርጋል፡፡ ይህ አሲድም በተመገብነው ምግብ ውስጥ ያሉ ፕሮቲኖች እንዲጠነክሩ አልፈጭ እንዲሉ ያደርጋቸዋል፡፡

2. #አያጭሱ
ምግብ ከተመገቡ በኋላ ወዲያው ሲጋራ ማጨስ አደገኛ ነው ከምግብ በኋላ የሚያጨሱ ሰዎች በሣንባ ካንሰር የመያዝ እድላቸው ከፍተኛ ነወ፡፡

3. #ፍራፍሬ አይመገቡ ከምግብ በኋላ ወዲያውኑ ፍራፍሬ መመገብ አንጀታችን ወዲያውኑ በአየር እንዲወጣጠር ያደርገዋል፡፡ፍራፍሬ መብላት ከፈለጉ፤ምግብ ከመመግብዎ ከአንድ ሰአት በፊት ወይም ከተመገብዎ ከአንድ ሰአት ተኩል በኋላ ቢሆን ይመረጣል፡፡

4. #ገላዎን አይታጠቡ ምግብ ከተመገቡ በኋላ ወዲያውኑ ገላን መታጠብ በእግርና በጃችን አካባቢ የደም ፍሰት (ዝውውር) መጠኑ እንዲጨምር የሚያደርግ ሲሆን በሆዳችን ያለው አካባቢ የደም ፍሰት ይቀንሰዋል፡፡በዚም ምክንያት የምግብ ስልቀጣ ይዳከማል፡፡

5. #ቀዝቃዛ ውሃ አይጠጡ ከምግብ በኋላ ቀዝቃዛ ውሃ ከበላነው ምግብ ውሰጥ የሚገኙት ዘይት ነክ ነገሮች ወደ ጠጣርነት ይቀየራቸዋል፡፡ ይህ ደግሞ የምግብ መፍጨት ከመጓተቱም በላይ ወደ ጠጣርነት የቀየረውን ዘይት እና ቅባት ጨጓራ ውስጥ የሚገኝ አሲድ ጋር በማገናኘት በፍጥነት ተሰባብሮ ወደ አንጀት ውስጥ እንዲገባ ያደርገዋል፡፡ይህም ወደ ስብነት ተቀይሮ ለካንሰር ሰበብ መጋለጥ ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ በተቻለ መጠን ከምግብ በኋላ ቀዝቃዛ ውሃ ከመጠጣት ይቆጠቡ፡፡ በምትኩ ለብ ያለ ውኃ መጠጣት የምግብ ልመት ስርአጡ የተሳካ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡

6. #የእግር ጉዞ አያድርጉ ከምግብ በኋላ ወዲያውኑ የእግር ጉውዞ ማድረግ የምግብ ስልጠቃ ሂደት በአግባቡ እንዳይከናወን ያደርገዋል፡፡

7. #ወዲያውኑ አይተኙ በልተን ወዲያውኑ ከተኛን የተመገብነው ምግብ በአግባቡ አይፈጭም፡፡ ይህ ደግሞ ለጨጓራ ህመምን ለአንጀት ቁስለት ይዳርጋል፡፡

ጤናና ሰላም ከናንተ ጋር ይሁን

ምንጭ:- ጠቅላላ ዕውቀት ጥያቄና መልስ General Knowledge

08/10/2025

‎ማንኛውም ዓይነት ተቀናናሽ ሰራተኛው በማመልከቻ ፈርሞ ካልፈቀደ በስተቀር ከወርሃዊ ደመወዙ ላይ መቀነስ የተከለከለ ነው [ ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ] 🤞

‎"ከሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ጋር መግባባት ላይ የተደረሰው ከመስከረም 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የተስተካከለው ጭማር በመስከረም ወር መጨረሻ ከሚከፈለው የመስከረም ወር ደመወዝ ጋር እንዲከፈል መንግስት አመራር የሰጠ መሆኑን ነው። ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከመስከረም ወር ደመወዙ ጋር አብሮ ባይከፈል እንኳን የመስከረም ወሯ ጭማሪ መጠን በጥቅምት ወር ውስጥ ይከፈላል። ማንኛውም ዓይነት ተቀናናሽ ባለመብቱ በማመልከቻ ፈርሞ ካልፈቀደ በስተቀር ከወርሃዊ ደመወዙ ላይ መቀነስ የተከለከለ መሆኑን በመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 በግልጽ ተደንግጓል። በሌላ በኩል ደግሞ ብዞዎቻችሁ በንግዱ ህብረተሰብ በኩል ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር ስጋታችሁን ገልጻችኋል። የተወሰኑት ካልሆነ በስተቀር ሁሉም ተመሳሳይ ተግባር ይፈጽማሉ ብለን አንጠብቅም። እነዚህንም ቢሆን ጥብቅ ክትትል እንደሚደረግባቸው ከክቡር የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚንስትር ጋር ተነጋግረናል።"

‎ዶ/ር መኩሪያ ኃይሌ-የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር

ይንን ገጽ ማድረግ አይርሱ🙏

06/10/2025
04/10/2025

#የተጣራ
የደሞዝ ጭማሬውና በአዲሱ ግብር ፣ ጡረታ በአጠቃላይ ተቀናንሶ የሚደርሳችሁ የተጣራ ደሞዝ
The Ethiopian Economist View መረጃውን አጋርቷል

እውነት ይሆን?
04/10/2025

እውነት ይሆን?

30/08/2025

ከመቀጠር በሚገኝ ገቢ ላይ ተፈጻሚ የሚሆኑት መጣኔዎች

ነሐሴ 20/2017 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በወጣ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 ላይ ከመቀጠር በሚገኝ ገቢ ላይ ተፈፃሚ የሚሆኑ የግብር መጣኔዎች ተቀምጠዋል፡፡

በመቀጠር በሚገኝ ወርሃዊ ገቢ ላይ ለሚጣለው ግብር ተፈጻሚ የሚሆኑት መጣኔዎች የሚከተሉት ናቸው፦

፡-
#በድረ-ገጽ_እና_ማኅበራዊ_ሚዲያ፡-
🌐 ድረ ገጽ፦ www.mor.gov.et
🌐 ቴሌግራም፦ https://t.me/MoREthiopiaOfficial/169
🌐 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/ERCA.info
🌐 ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/
🌐 ቲክቶክ፡- tiktok.com/
፡-
📺 ፋና ቴሌቪዥን ሐሙስ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
📺 ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን /ኢ.ቢ.ሲ/ ቅዳሜ ማታ ከ2፡00 ዜና በኋላ፣
፡-
📻 ፋና ኤፍ ኤም ሬድዮ 98.1 ሐሙስ ማታ ከ2፡30 ጀምሮ፣
📻 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሬድዮ 93.1 ማክሰኞ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ፣
፡-
📑 በገቢ ለልማት ወርሃዊ ጋዜጣ እንዲሁም
☎ በነጻ ጥሪ አገልግሎታችን፡- 8199 ላይ በነፃ በመደወል መረጃዎችን ማግኘት ይችላሉ፡፡

Address

Assosa
Asosa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሙሐመድTour&trave posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሙሐመድTour&trave:

Share

Category