Amhara Culture & Tourism Bureau

Amhara Culture & Tourism Bureau Government organization

በችግር ውስጥ ኾኖም አበረታች የቱሪዝም ሥራዎች ተከናውነዋል።=========+++======ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 12/2017 ዓ.ም  የአማራ ክልል ምክር ቤት የሰው ሃብት አሥተዳደር እና ቱሪዝም ...
19/07/2025

በችግር ውስጥ ኾኖም አበረታች የቱሪዝም ሥራዎች ተከናውነዋል።
=========+++======
ባሕር ዳር፡ ሐምሌ 12/2017 ዓ.ም የአማራ ክልል ምክር ቤት የሰው ሃብት አሥተዳደር እና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሥሩ የሚቆጣጠራቸውን እና የሚደግፋቸውን ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም እየገመገመ ይገኛል።1

የባሕል እና ቱሪዝም ቢሮ ኀላፊ መልካሙ ጸጋዬ የክልሉ ባሕል እና ቋንቋ አጠቃቀም እንዲያድግ እንደ ሻደይ፣ አሸንድዬ፣ ሶለል እና የመሳሰሉ ትውፊቶችን እና ክዋኔያቸውን በአግባቡ ማከናዎናቸውን በአብነት አንስተዋል።

የክልሉን ባሕል ለማሳደግ በጎንደር ከተማ "ድንቅ ባሕል፤ ድንቅ ምድር " በሚል ርዕስ ክልላዊ ፌስቲባል ተደርጓል ያሉት ቢሮ ኀላፊው በዚህም በክልሉ ከሚገኙ 22 ዞኖች ውስጥ 18ቱን አሳታፊ ማድረግ ተችሏል ነው ያሉት።

በዚህ ፌስቲባል ላይ የአፋር እና የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የባሕል ቡድኖች እንዲሳተፉ በመጋበዝም ዘርፈ ብዙ ጥቅም ተገኝቷል ብለዋል ቢሮ ኀላፊው።

የአማራ ክልል የበለጸገ የባሕል ባለቤት ቢኾንም የተጠናከረ የሽምግልና ማኀበር አልነበረውም ያሉት አቶ መልካሙ ለሰላም እና ለባሕል እሴት ግንባታ በክልሉ ካሉት 22 ዞኖች የተመረጡ ሽማግሌዎችን በማኀበር ለማቀፍ ተሠርቷል ነው ያሉት።

በክልሉ ውስጥ በባሕል ኢንዱስትሪው ውስጥ ለተሰማሩ የዕደ ጥበብ ባለሙያዎች የገበያ ትስስር በመፈጠሩ ምርታቸውን ለውጭ ሀገር እንዲያቀርቡ አስቻይ ኹኔታዎች መመቻቸታቸውን ቢሮ ኀላፊው ተናግረዋል።

ቢሮው የሀገር በቀል ዕውቀትን ለማስፋፋት ተግቶ እየሠራ ነው ያሉት አቶ መልካሙ የብራና ሥራ ሥልጠና ተሰጥቷል። አንባቢ ትውልድን ለመፍጠርም በክልሉ በበርካታ አካባቢዎች ቤተ መጻሕፍቶች እየተስፋፉ ነው፤ በግብዓት እየተሟሉም ይገኛሉ ነው ያሉት።

የቱሪዝም መሠረተ ልማት አቅርቦትን በማስፋፋት የኀብረተሰብ ተሳትፎን ማሳደግ ስለመቻሉም አስረድተዋል።

የዘጌ ባሕረ ገብ መንገድን በመሥራት ለቱሪስቶች ምቹ የማድረግ ሥራ መከናወኑንም አውስተዋል።

እንደ ሀገር በተገነባው አንድነት ፖርክ ውስጥ የአማራ ክልልን ሕዝብ በወጉ እና የሥራውን ያህል ወካይ የኾነ የለውም የሚለውን ቅሬታ በመገንዘብ እና ትኩረት በመስጠት ወካይ ዲዛይን ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ተገብቷል ብለዋል።

የክልሉን የመስህብ ሃብት ለማስተዋወቅ መደበኛ የመገናኛ ብዙኅንን እና ማኀበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም ሰፊ ሥራ ተሠርቷል፤ በዚህም አበረታች ውጤት ተገኝቶበታል ነው ያሉት።

ከ5 ሚሊዮን በላይ የሀገር ውስጥ እና ከ27 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ቱሪስቶች ክልሉን የጎበኙት በተከናወነው የማስተዋወቅ ሥራ መኾኑን አንስተዋል።

ቢሮ ኀላፊው በክልሉ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋርም ትብብር ዐውደ ጥናት በማቅረብ ጥሩ ግብዓት ተገኝቷልም ብለዋል።

ዘገባው: የአሚኮ ነው።

"ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!
Amhara Culture & Tourism Bureau

# Visit Amhara
ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የፌስቡክ ገጻችንን ይወዳጁ ያድርጉ 👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100057096864608&mibextid=ZbWKwL

በክልሉ መስህቦችን ከጎበኙ ቱሪስቶች ከ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ!===========+++=======በአማራ ክልል በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት መስህቦችን ከጎበኙ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱ...
18/07/2025

በክልሉ መስህቦችን ከጎበኙ ቱሪስቶች ከ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኘ!
===========+++=======
በአማራ ክልል በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት መስህቦችን ከጎበኙ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘት መቻሉን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የስራ ክንውን የግምገማ መድረክ ሃምሌ 11/2017 ዓ.ም በባሕር ዳር ከተማ ተካሄዷል።

በመድረኩ የቢሮው ኃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋዬ እንደገለጹት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ12 ሚሊዮን በላይ የሀገር ውስጥና ከ27 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ቱሪስቶች ክልሉን ጎብኝተዋል።

ባለድርሻ አካላትን፣ የቢሮውን መዋቅር ከላይ እስከታች በማቀናጀትና መገናኛ ብዙሃንን በአግባቡ በመጠቀም በተከናወነው የማስተዋወቅ ስራ የቱሪዝም ዘርፉን በማነቃቃት ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች የቱሪዝም ፍሰቱ ከታቀደው በላይ የላቀ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚቻል የታየበት እንደሆነም አመልክተዋል።

የክልሉን ዕምቅ የባህልና የቱሪዝም አቅም በማስተዋወቅና መዳረሻዎችን በማልማት የተከናወነው ስራ ጨምሮ በበጀት ዓመቱ 5 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘት እንደተቻለ አስታውቀዋል።

የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ስራዎች፤ በባህል ልማትና እሴት ግንባታ በኩልም ሰፊ ስራ ተከናውኗል ብለዋል።

በተለይም በክልሉ በየዓመቱ በድምቀት የሚከበሩ የሻደይ፣ አሸንድዬ፣ ሶለል፣ የእንግጫ ነቀላና የቡሄ በዓላትን የቱሪዝም መዳረሻ የማድረግ ስራ በስፋት መከናወኑንም ኃላፊው ገልጸዋል።

"ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!
Amhara Culture & Tourism Bureau

# Visit Amhara
ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የፌስቡክ ገጻችንን ይወዳጁ ያድርጉ 👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100057096864608&mibextid=ZbWKwL

በቅንጅትና በትብብር መስራታችን በበጀት ዓመቱ ውጤታማ ስራ እንድንሰራ አድርጎናል፡፡ አቶ መልካሙ ፀጋዬ የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ:=============+++=========ባህር ዳር፤...
18/07/2025

በቅንጅትና በትብብር መስራታችን በበጀት ዓመቱ ውጤታማ ስራ እንድንሰራ አድርጎናል፡፡ አቶ መልካሙ ፀጋዬ የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ:
=============+++=========

ባህር ዳር፤ ሃምሌ 11/2017 ዓ.ም
የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም የቢሮው ጠቅላላ ባለሙያዎች፣ ተጠሪ ተቋማትና ሌሎች ተሳታፊዎች በተገኙበት ሃምሌ 11/2017 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ ገምግሟል፡፡ በግምገማ መድረኩ የቢሮው የ2017 በጀት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት በቢሮው የዕቅድ እና በጀት ዝግጅት ክትትልና ግምገማ ዳይሬክተር በአቶ መላኩ ብርሃኔ ቀርቧል፡፡

በዕለቱ ተጠሪ ተቋማትም /ሙሉዓልም የባህል ማዕከል እና የአማራ ህዝብ ዝክረ- ታሪክ ማዕከል/ የበጀት ዓመቱን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል፡፡
በሁሉም በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ውይይት ተደረጎባቸው አስተያየትም ተሰጥቶባቸዋል፡፡

ተሳታፊዎችም በበጀት ዓመቱ በርካታ ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ ከባለድርሻ እና አጋር አካላት ጋር ተቀራርቦና ተግባብቶ መስራት ውጤታማ ስለሚያደርግ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተሣታፊዎች አስተያየታቸውን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይ የሃገር በቀል ዕውቀቶች ላይ በትኩረት መስራት ይገባልም ተብሏል፡፡በበጀት ዓመቱ ማከናወን እያለብን ያላከናወናቸው ሁነቶችና ፕሮጀክቶች በ2018 በጀት ዓመት በትኩረት ልንሰራቸው ይገባል ሲሉም ተሣታፊዎች አስተያየታቸውን ገልጸዋል፡፡

ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር የሚደረገው ትብብር፣ ቅንጅታዊ አሰራርና የመግባቢያ ሰንድ መፈራረም ውጤታማ ስላደረገን በተለይ በሰው ሃብት ልማቱ ላይ ከፍተኛ የሆነ ለውጥ ስለሚያመጣ በቀጣይም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በውይይቱ ተነስቷል።

በበጀት ዓመቱም የካፒታል ፕሮጀክቶች ከምንጊዜውም በላይ በተሻለ ሁኔታ የተፈጸሙ መሆናቸው በግምገማ መድረኩ ተነስቷል፡፡ የቅርስ ጥበቃና እንክብካቤ ስራውን የበለጠ ውጤታማ ሊያደርገው የሚችለው የኖራ ፋብሪካ ስራ እንቅስቃሴም በበጀት ዓመቱ ከተሰሩት ውስጥ በዋናነት የሚጠቀስና በቀጣይም በልዩ ሁኔታ መሰራት ያለበት መሆኑ ተገልጿል፡፡

የባህልና ቱሪዝም ዘርፍ በባህሪው ቅንጅታዊ አሰራርንና መተባበርን ስለሚጠይቅ በቅንጅትና በትብብር መስራታችን በበጀት ዓመቱ ውጤታማ አድርጎናል ሲሉ አቶ መልካሙ ፀጋዬ የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ተናግረዋል፡፡ አመራሩና ባለሙያው እንዲሁም ቢሮው ከሌሎች ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በቅንጅት ከሰራ ውጤታማ መሆን ይቻላል ብለዋል ቢሮ ኃላፊው፡፡ በበጀት ዓመቱ ከፌደራል ሚኒስተር መስሪያ ቤቶች ጋርም የተሻለ ግንኙነት እንደነበረም ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ አቶ መልካሙ አክለውም እንደነዚህ ዓይነት መድረኮችን ማካሄዳችን ጥንካሬዎቻችንና ስኬቶቻችን እንድናስቀጥላቸው እና ድክመቶቻችን እና ክፍተቶቻችን ደግሞ በግልጽ አይተን መፍትሄ እንድናስቀምጥላቸው ይረዳሉ ብለዋል፡፡

በተያዘው በጀት ዓመትም /የ2018 ዓ.ም/ በቅንጅት፣ በመነጋገርና በመቀራረብ ውጤታማ ስራ በመስራት የዘርፉን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ማሳደግ ይኖርብናል ብለዋል የቢሮ ኃላፊው አቶ መልካሙ ፀጋዬ፡፡

"ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!
Amhara Culture & Tourism Bureau

# Visit Amhara
ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የፌስቡክ ገጻችንን ይወዳጁ ያድርጉ 👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100057096864608&mibextid=ZbWKwL

በቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎች ላይ እሴት በመጨመር የጎብኝዎችን ቁጥር መጨመርና የቆይታ ጊዜን ማራዘም እንደሚቻል ተገለጸ!==========+++==========የዘጌ ባህረ ገብ የቱሪዝም መዳረሻ የቱ...
18/07/2025

በቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎች ላይ እሴት በመጨመር የጎብኝዎችን ቁጥር መጨመርና የቆይታ ጊዜን ማራዘም እንደሚቻል ተገለጸ!
==========+++==========

የዘጌ ባህረ ገብ የቱሪዝም መዳረሻ የቱሪስት እግረኛ መንገድ እና በደቅ ደሴት የቅድስት አርሴማ ወደብና የመንገድ ግንባታ ስራ በማጠናቀቅ ለጎብኝዎች ምቹ ማድረግ እንደተቻለ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋዬ በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ወቅት ገልፀዋል።
በበጀት ዓመቱ በተደረጉ ሁሉን አቀፍ የቱሪዝም ልማትና የፕሮሞሽን ተግባራት 27,010 የውጭ እና 12,711,565 የአገር ውስጥ በድምሩ 12,738,575 ቱሪስቶች የክልላችንን መስህብ ሃብቶችን በመጎብኘት እና ክብረ በዓላት ላይ በመሳተፍ ብር 258,329,881 ከውጭ ሀገር ጎብኝ እና 5,581,206,034 ብር ከሀገር ውስጥ በድምሩ ብር 5,839,535,915 ገቢ መገኘቱን የቢሮ ኃላፊው ጨምረው ገልፀዋል።

በመጨረሻም በቱሪዝም መዳረሻ ቦታዎች ላይ እሴት በመጨመር የጎብኝዎችን ቁጥር መጨመርና የቆይታ ጊዜን ማራዘም እንደሚቻል ቢሮ ሃላፊው አቶ መልካሙ ጸጋዬ ገልጸዋል።

"ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!
Amhara Culture & Tourism Bureau

# Visit Amhara
ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የፌስቡክ ገጻችንን ይወዳጁ ያድርጉ 👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100057096864608&mibextid=ZbWKwL

የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፁም ግምገማ አካሄደ:-=========+++======ባህር ዳር፡ ሃምሌ 11/2017 ዓ.ምየአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የ2017 ...
18/07/2025

የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፁም ግምገማ አካሄደ:-
=========+++======
ባህር ዳር፡ ሃምሌ 11/2017 ዓ.ም
የአብክመ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፁም ግምገማ የቢሮው ኃላፊ አቶ መልካሙ ፀጋዬ ፣የተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎችና ተወካዮች እና የቢሮው ባለሙያዎች በተገኙበት ሃምሌ 11/2017 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ እየገመገመ ነው።
የእቅድ አፈፃፀም መገምገማችን የነበሩንን ጠንካራ ጎኖች የበለጠ አጣናክረን እንድንቀጥል እና ድክመቶችን ለማስተካከል ያግዛል ሲሉ የቢሮው ኃላፊ በመክፈቻ ንግግራቸው ገልፀዋል።

"ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!
Amhara Culture & Tourism Bureau

# Visit Amhara
ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የፌስቡክ ገጻችንን ይወዳጁ ያድርጉ 👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100057096864608&mibextid=ZbWKwL

በአማራ ክልል ከሚገኙ ብሐራዊ ፓርኮች መካከልቦረና ሳይንት ወረሂመኑ፣ ጎደቤ እና አልጣሽ ብሔራዊ ፓርኮች
16/07/2025

በአማራ ክልል ከሚገኙ ብሐራዊ ፓርኮች መካከል
ቦረና ሳይንት ወረሂመኑ፣ ጎደቤ እና አልጣሽ ብሔራዊ ፓርኮች

የጣና ሐይቅ ዘውድ፤ የቱሪዝም ሰገነት ! 🇪🇹የሀገር ሀብት፣ የጣና ሐይቅ ዘውድ እና የቱሪዝም ሰገነት ናት ጣና ነሽ ፪ የቱሪስት ጀልባ፡፡ ጀልባዋ የሀገሯን ሜዳና ተራራውን፣ ሸለቆና ሸንተረሩን...
16/07/2025

የጣና ሐይቅ ዘውድ፤ የቱሪዝም ሰገነት !
🇪🇹
የሀገር ሀብት፣ የጣና ሐይቅ ዘውድ እና የቱሪዝም ሰገነት ናት ጣና ነሽ ፪ የቱሪስት ጀልባ፡፡ ጀልባዋ የሀገሯን ሜዳና ተራራውን፣ ሸለቆና ሸንተረሩን፣ ከተማና ገጠሩን ሁሉ እያቆራረጠች ለቱሪዝሙ ሰንደቅ ልትሆን ወደ እልፍኟ እየተቃረበች ነው።

በየደረሰችበት አካባቢ ደማቅ አቀባበል እየተደረገላት፣ በመንገዷ የኢትዮጵያ ልጆች በተስፋና በደስታ እየሸኟት፤ እሷም የአንድነት ሰበዝ መንገደኛ ሆኗ፤ ህዝብም እንዲኮራ ሀገርም ይደሰት ዘንድ ጣና ነሽ ፪ ቱሪዝምን ከባህር ላይ ትራንስፖርት ጋር አጣምራ ልትሰጥ ተቃርባለች፡፡

ጣና ነሽ ፪ በመንገዷ የወንድማማችነትና የእህትማማችነት መንፈስን በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ እየናኘች ነው፡፡ በየደረሰችበት አካባቢ ያለው የህዝብ አቀባበል የሚነግረን ይህን ነው፡፡ ጀልባዋ ባለፈችባቸው ስፍራዎች ሁሉ ከተለዋጭ መንገዶች ዝግጅትና ዳርቻዎች ማስፋት እስከ የመብራት መቁረጥና ሌሎችም የትራፊክ ዝውውር ውስንነቶችን ጋር ተያይዞ ሲያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን ለመፍታት እየታየ ያለ ኢትዮጵያዊያን ህብረትና መተጋገዝ ልዩ ነው፡፡ ይህም ጣና ነሽ ኢትዮጵያዊያንን በወንድማማችነትና በእህትማማችነት ጎዳና ያሰለፈች የአንዱን ችግር አንዱ እንዲረዳና በእኔነት ስሜት በአንድነትም እንዲፈታ አብነት የሆነች የሀገራዊ አንድነት ጌጣችን ናት፡፡

በእልህ አስጨራሽ ጉዞዋ ትዕግስትን፣ ውጣ ውረድን በብቃት የማለፍ አብነት ሁናለች። ጣና ነሽ ፪ የቱሪስት ጀልባ በቅርቡ የብሔራዊነት ሰንደቅ ሁና ጣና ሀይቅ ላይ ትንሳፈፋለች። በጉዞዋ ከብልፅግና ጋር ብትችል አብረህ ሩጥ ካልሆነ አብረህ ተራመድ ካልቻልክ እየዳህክም ቢሆን አብረህ ሂድ ይህም ካልሆነልህ እንደ እባብ ተሰበህ ተከተል እንጅ የሀገርህ እሾህ አትሁን የሚል ፍልስፍናን በከተማና በገጠር እየናኘች ይመስላል።

ውስብስቡ የጣና ነሽ ፪ የቱሪስት ጀልባ ጉዞ ለትውልዱ ዘረፈ ብዙ ትምህርት የሚሰጥ ነው። የመጀመር፣ ሳይሰለቹ የመጓዝ፣ በመንገድ የሚያጋጥሙ እንቀፋቶችንና ፈተናዎችን ሁሉ በትብብር በፅናት የማለፍ፣ የመሻገር፣ የመከናወን፣ የማንሰራራት ዘመን ጅማሮ ምሳሌ ናት።

ጣናነሽ ለጀልባ ባልተሰራ መንገድ እያለፈች ነው። ኢትዮጵያችንም አሁን እያሳለፈችው ያለው ፈተና እንዲሁ እያለፈ ትክክለኛ ከፍታዋ ላይ ደርሳ እስክትንሳፈፍ ድረስ ሰይፍም ሰልፍም ያነሱባት ጠላቶቿ ፈተናዎችን ቢያበዙባትም በድል ላይ ድልን እየተጎናጸፈች ጉዞዋን ቀጥላለች።

ሰቆጣ ለሻደይ በዓል ዝግጅት ጀምራለች።==========+++======== ሻደይ በዋግ ኽምራ ልዩ ትርጉም ያለው የልጃገረዶች ጨዋታ ነው። ሻደይ ከነሃሴ 16 እስከ 21 ድረስ በየዓመቱ በልዩ ል...
15/07/2025

ሰቆጣ ለሻደይ በዓል ዝግጅት ጀምራለች።
==========+++========

ሻደይ በዋግ ኽምራ ልዩ ትርጉም ያለው የልጃገረዶች ጨዋታ ነው። ሻደይ ከነሃሴ 16 እስከ 21 ድረስ በየዓመቱ በልዩ ልዩ የባሕል አልባሳትና ጌጣጌጦች የተዋቡ ልጃገረዶች በድምቀት የሚያከብሩት በዓል ነው።

በመኾኑም የሻደይን በዓል በልዩ ኹኔታ ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራ መጀመሩን የሰቆጣ ከተማ አሥተዳደር ባሕልና ቱሪዝም ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ካሳ ከበደ ገልጸዋል።

የሻደይ ባሕላዊ ጨዋታ ከኦሪት ጀምሮ ሲከበር እንደመጣ ይነገራል። በዓሉን በዞን ደረጃ ከ20ዐዐ ዓ.ም ጀምሮ በሰቆጣ ከተማ ከየወረዳው የተውጣጡ ልጃገረዶች የሚያከብሩት በዓል እንደኾነ ኀላፊው ተናግረዋል።

ሰቆጣ ከተማም በዓሉን በድምቀት ለማክበር ከወጣቱ፣ ከነጋዴው ማኅበረሰብ እና ከአመራሩ ጋር የጋራ ሥራ መጀመራቸውንም ጠቁመዋል።

የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ባሕልና ቱሪዝም መሥሪያ ኃላፊ ኢዮብ ዘውዴ የሻደይ ባሕላዊ ጨዋታ በታዳጊዎች፣ በአዋቂ ልጃገረዶች እና በእናቶች ተከፍሎ የሚከበርና የዋግ ሕዝብ ልዩ መገለጫ ነው።

ወጣቶችም የሰቆጣ ከተማን ለእንግዶች ምቹ እንድትኾን ለማድረግ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት በእቅድ በማካተት ወደ ተግባር ተገብቷል። በአካባቢው ያለውን ሰላም በማጽናት ለእንግዶች የተመቼ ከባቢ ለመፍጠር በጋራ መሥራት ይገባል ነው ያሉት አቶ ኢዮብ።

ሻደይን ከነሃሴ 01 ጀምረው ልጃገረዶች አልባሳት በማሟላት፣ እንሶስላ በመሞቅ እና ሻደይ በመንቀል፣ ባሕላዊ ጨዋታዎችንም በቡድን መለማመድ ይጀምራሉ።

መምሪያ ኀላፊው እንዳሉት እንደ ዞን በዓሉን በድምቀት ለማክበር ኮሚቴ በማዋቀር እና ተልዕኮ በመሥጠት ወደ ሥራ ተገብቷል።

ወጣቶችም የአካባቢውን ሰላም ከመጠበቅ ባሻገር ውብና ጽዱ ከተማን ለመፍጠር በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጠይቀዋል።

የደንቀዝ ቤተ መንግስት  =======+++=====ደንቀዝ ቤተ መንግስት በጎንደር ዙሪያ ወረዳ ከማክሰኝት ከተማ በደጎማ መስመር 28 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ታሪካዊ ቤተ መንግስት ነው፡፡ ቤተ...
12/07/2025

የደንቀዝ ቤተ መንግስት
=======+++=====
ደንቀዝ ቤተ መንግስት በጎንደር ዙሪያ ወረዳ ከማክሰኝት ከተማ በደጎማ መስመር 28 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ታሪካዊ ቤተ መንግስት ነው፡፡ ቤተ መንግስቱ በ1620ቹ የመጀመሪያ ዓመታት በአጼ ሱስንዮስ የተሰራ ሲሆን አካባቢውን ለመቃኘት ከሚያስችልና በወይራ ዛፍ በተከበበ ማራኪ አምባ ላይ ይገኛል፡፡

አጼ ሱስንዮስ ጎመንጌ አፋፍ ደንቀዝ ላይ ቤተ መንግስት ማሰራታቸው ከአጼ ሰርፀ ድንግል ጀምሮ ሲነገር የነበረውን “ጎ ትነግስ” ንግርት ለመፈጸም እንደነበር ይነገራል፡፡ “ጎ ትነግስ” በ “ጎ” ፊደል በሚጀመር ቦታ ቤተ መንግስቱን የተከለ ንጉሥ መንግስቱ ይረጋል ተብሎ ሲነገር የነበረ አፈ-ታሪክ ነው፡፡

አጼ ሱስንዮስ በደንቀዝ ሁለት የተለያዩ ህንጻዎችን ነበር ያስገነቡት፡፡ የመጀመሪያው ባለሁለት ፎቅ እና ምድር ቤት የነበረው የቤተ መንግስቱ ህንጻ ሲሆን የተለያ አገልግሎት የሚሰጡ ክፍሎች ነበሩት፡፡ ዛሬም የቤተ መንግስቱ ፍርስራሽ በቦታው ይገኛል፡፡ ሁለተኛው ከቤተ መንግስቱ በግምት 250 ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ በመስቀል ቅርጽ የተሰራ ቤተ ክርስቲያን እንደነበር የሚታመን ህንጻ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ በውስጡ የሚገኙ ልዩ ልዩ ምልክቶችን በማየት ምንአልባትም በወቅቱ ለነበሩ ካቶሊኮች ሲጠቀሙበት የነበረ ሊሆን እንደሚችል የታሪክ ምሁራን ይናገራሉ፡፡

ቡልጋድንቅ ምድር!ስለ ቡልጋ ምን ያውቃሉ? ቡልጋ ሲባል ወደ አዕምሮዎ ምን ይመጣል? ሀሳብዎትን ያካፍሉ።"ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!Amhara Culture & Tourism Bureau   ...
11/07/2025

ቡልጋ

ድንቅ ምድር!

ስለ ቡልጋ ምን ያውቃሉ? ቡልጋ ሲባል ወደ አዕምሮዎ ምን ይመጣል? ሀሳብዎትን ያካፍሉ።

"ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!
Amhara Culture & Tourism Bureau

# Visit Amhara
ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የፌስቡክ ገጻችንን ይወዳጁ ያድርጉ 👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100057096864608&mibextid=ZbWKwL

የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ የጉምሩክ ከተማ። =======+++============== "ጠላት መጣ መሰል ተንጫጩ ወፎቹ   ጀግኖች ይጠሩልን አልዩ አምባዎቹ" ተብሎ የተገጠመላት፣ የበረሃዋ ገነት በ...
11/07/2025

የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ የጉምሩክ ከተማ።
=======+++==============
"ጠላት መጣ መሰል ተንጫጩ ወፎቹ
ጀግኖች ይጠሩልን አልዩ አምባዎቹ"
ተብሎ የተገጠመላት፣ የበረሃዋ ገነት በመባል የምትታወቀው ውቢቷ አልዩ አምባ ዛሬም በታሪኳ ትዘከራለች።

የአንኮበር ታሪክ ሲነሳ፣ የስምጥ ሸለቆ አካል የኾነችው እና የመጀመሪያዋ የኢትዮጵያ የንግድ ማዕከል የነበረችው አልዩ አምባ ሁሌም ትጠቀሳለች።

በሰሜን ሸዋ ዞን አንኮበር ወረዳ የምትገኘው አልዩ አምባ የተመሠረተችው በ1266 ዓ.ም እንደኾነም ይነገራል ስያሜዋንም ያገኘችው "አልየ" ከተባለ የአካባቢው ነጋዴ እንደኾነ ታሪክ ይነግረናል።

ከአዲስ አበባ 187 ኪሎ ሜትር፣ ከደብረ ብርሃን 57 ኪሎ ሜትር፣ ከአንኮበር ወረዳ ዋና ከተማ ጎረቤላ ደግሞ 15 ኪሎ ሜትር ትርቃለች ይህችው ድንቅ ስፍራ።

አልዩ አምባ ለረዥም ርቀት ንግድ (ሲራራ ንግድ) ምቹ በመኾኗ በወቅቱ እስከ ዘይላ ወደብ ድረስ ተዘርግቶ የነበረው የሲራራ ንግድ ማዕከል በመኾንም አገልግላለች።

በ1834 እና 1835 ዓ.ም በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የኾነው የቀረጥ ውል በአልዩ አምባ ገበያ መሠረት ተፈርሟል።

በአጼ ምኒልክ ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ የቀረጥ መሥሪያ ቤት ሲከፈት በአልዩ አምባ የጉምሩክ ጽሕፈት ቤት ሥራውን የጀመረ ሲኾን ከዘይላ ወደብ በኩል ወደ ኢትዮጵያ በሚገቡ የንግድ ዕቃዎች ላይ የቀረጥ ክፍያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጀመረባት ከተማም ነች።

ከ1ሺህ 500 እስከ 1ሺህ 700 የሚጠጉ ግመሎች የሀገር ውስጥ ሸቀጦችን ወደ ውጭ ያጓጉዙባት እንደነበርም ይነገራል።

በአሁኑ ወቅት የአማራ፣ የአፋር እና የአርጎባ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች በፍቅር እና በአንድነት የሚኖሩባት ድንቅ ቦታም ናት አልዩ አምባ።

በ19ኛው ክፍለ ዘመን የንግድ ማዕከል በነበረችበት ወቅት አራት መግቢያ እና መውጫ በሮች የነበሯት ይህችው ድንቅ ስፍራ በሮቿም አዋሽ በር (ጨው፣ ሻይና ሌሎች ሸቀጦች ከዘይላ ወደብ የሚገቡበት) እና ጨኖ በር በመባል የሚታወቀው በር ሌላው መግቢያ በር ነው።

ይህችው ድንቅ ስፍራ መውጫ በሮችም ነበሯት ይኸውም አንኮበር በር (ከመሀል ሀገር እስከ ሰሜን ዕቃዎች የሚላኩበት) እና ምንጃር በር (ወደ ደቡብ ሸቀጦች የሚላኩበት) ናቸው።

አልዩ አምባ ከፐርሺያ፣ ከሕንድ እና ከአረብ ሀገሮች የሚመጡ በርካታ የውጭ ዜጎች ይኖሩባት እንደነበርም ጎብኝዎች ጽፈዋል።

ስልክ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ከእንጦጦ እስከ አልዩ አምባ ድረስ መስመር ተዘርግቶለት ነበር፤ እስካሁንም "ስልክ አምባ" የሚባል ሰፈር መኖሩ የዚሁ ማሳያ ነው።

አሁን ላይም አልዩ አምባ የንግድ እንቅስቃሴ በሰፊው የሚካሄድባት ታሪካዊ ከተማም ናት።

ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!
Amhara Culture & Tourism Bureau

# Visit Amhara
ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የፌስቡክ ገጻችንን ይወዳጁ ያድርጉ 👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100057096864608&mibextid=ZbWKwL

በአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ  እየተገነባ የሚገኘው የዘጌ ባህረገብ የቱሪስት መዳረሻ እግረኛ መንገድ ግንባታ በምስል፡፡      "ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!Amhara Culture ...
11/07/2025

በአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ እየተገነባ የሚገኘው የዘጌ ባህረገብ የቱሪስት መዳረሻ እግረኛ መንገድ ግንባታ በምስል፡፡

"ድንቅ ምድር- አማራ"ን ይጎብኙ!
Amhara Culture & Tourism Bureau

# Visit Amhara
ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ የፌስቡክ ገጻችንን ይወዳጁ ያድርጉ 👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/profile.php?id=100057096864608&mibextid=ZbWKwL

Address

Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Culture & Tourism Bureau posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share