27/05/2026
የጎንደር አብያተ መንግስታትንና በዙሪያው የሚገኙ ቅርሶችን ለማስተዳደር የሰው ሀይል መዋቅር ጥናት ለውይይት ቀረበ።
የጎንደር ከተማ ዓለም አቀፍ ቅርስ የሆነው የአጼ ፋሲል አብያተ መንግስታት ቅጥር ግቢ አጠቃላይ ጥገና በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር ዓብይ አህመድ ተነሳሽነት ከተጠገነ በኋላ ለተፈጠረው ምቹ የጉብኝት አውድ እና የቱሪዝም መዳረሻውን የሚመጥን መዋቅር በማስፈለጉ ቅርሱን የማስተዳደር አቅም የሚፈጥር የሰው ሃይል ጥናት ለውይይት ቀርቧል።
በአብክመ ባህል፣ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ፣ አማራ ክልል ስቴት ዩኒቨርሲቲና በጎንደር ከተማ ባህልና ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ በኩል የተዘጋጀው ይህ ጥናት ከብርት ም/ከንቲባ ወ/ሮ ደብሬ የኋላ፣ የባህልና ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ማሪያሟ ካሳሁንና ከአብክመ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ቢሮ በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች፣ከአብክመ ገንዘብና ፕላንና ልማት ቢሮ ፣በተከማው ውስጥ የሚገኙ የባህልና የቱሪዘም ልዩ ልዩ አደረጃጀቶችና በላድርሻ አካላት በተገኙበት መድረክ የመዋቅር ጥናቱን ማቅረብ ተችሏል ።
በጎንደር ከተማ ውስጥና አካባቢው የሚገኙ የአብያተ መንግታትና ልዩ ልዩ ቅረሶችን በዘላቂነት ለማሰተዳደር የገቢ ምንጭ ለማሰደግና ለትውልድ ለማስተላለፍ የሚያስችል አደረጃጀት መፈጠር እንዳለበት በጥናቱም ከ96 ላይ የሰው ኃይል እንደሚያስፍልግ ቀርቧል።
ክብርት ም/ከንቲባ ወ/ሮ ደብሬ የኋላ ለቀረቡ ጥያቄዎች እና ሃሰቡች ምላሽ የሰጡ ሲሆን የሰው ሃይሉ አደረጃጀት ቅርሶቻቸን በዘላቂት ለመጠበቅና ለመንከባከብ ለተተኪ ትውልድ ለማስተላለፍ እንዲሁም ቅርሶችን በማስተዋወቅ የቱሪስት ፍሰቱን ለማሳደግ የኢኮኖሚ ፋይዳቸውን በማሳደግ የሚጫወተው ሚና ጉልህ መሆኑን ክብርት ም/ከንቲባዋ ጠቁመዋል።
የጎንደር ከተማ የባህልና ቱሪዝምና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ማሪያም ካሳሁን ተነሳሽነቱን ወስዶ ጥናቱን በማስጠናት ተግባራዊ እንዲሆን የክልሉን የባህልና ቱሪዝም ስፖርት ቢሮ እንዲሁም አመራሩን የሚያደርገው ድጋፍ ካመሰገኑ በኋላ ጥናቱ ዳብሮ በሥራ ላይ እንዲውል እንደ መምሪያ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርጉ አሳስበዋል።
የመዋቅር ጥናቱም የተሰጡ አስተያየቶችን በማካተትና በማዳበር የጋራ አመራር ተሰጥቶበት በቀጣይ ወደ ተግባራዊነት እንደሚገባ ተጠቁሟል ።።