20/08/2025
እናትነት!
ዛሬ ጀግና የሆኑ እናት እናስተዋዉቃችሁ፦ ከወላይታ!
የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢንጅነር ሀይለማርያም ደሳለኝ ወላጅ እናት ሲሆኑ ወልደው ለወግ ለማእረግ ካበቋቸው ልጆች መካከል
1/ የቀድሞ ጠ/ሚ/ር ክቡር ኢንጂነር ሀይለማርያም ደሳለኝ፣
2/ የኢትዮጵያ ሲቭል ሰርቪስ ዩንቨርስቲ ፕረዚዳንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ደሳለኝ፣
3/ የአድስ አበባ መንገድ ትራንስፖርት የመንገድ ደህንነት ኃላፊ ኢንጅነር ገነቱ ደሳለኝ፣
4/ የሀዋሳ ዩንቨርስቲ ሪፈራል ሆስፒታል መምህር ዶ/ር ብስራት ደሳለኝ፣
5/ የዱቦ ሆስፒታል ሰዉ ሀብት አመራር ዳይሬክተር አቶ መስፍን ደሳለኝ፣
6/ የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ም/ኃላፊ ዳዊት ደሳለኝ፣
7/ የፌደራል መንገድ ትራንስፖርት ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግሥት ደሳለኝ፣
8/ የግል ኢንቨስተር አቶ ማርቆስ ደሳለኝ እና ደረጄ ደሳለኝ እናትም፣ አባትም ሆነው ያሳደጉ ለኢትዮጵያ ያበረከቱ ጀግና ኢትዮጵያዊት እናት ናቸው!
በዛ ላይ እሳቸው ራሱ ዶክተር ናቸው!
እናት ሀገር ነች ሲባል በምክንያት ነው!
ረጅም ዕድሜ ከጤና ለእናታችን! 🥰🤲