Mizan Teferi Official

Mizan Teferi Official Mizan Teferi is a Town and the Administrative Center, of the Bench Sheko Zone in the South West Ethiopia Peoples' Region of Ethiopia.

Located about 160 kilometers southwest of Jimma,

በሚዛን አማን ከተማ  ዛሬ ማለዳ የከተማ አስተዳደር አመራሮችን ጨምሮ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል ሚዛን አማን ግንቦት 23/2017 ዓ/ም በሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ተከታ...
01/06/2025

በሚዛን አማን ከተማ ዛሬ ማለዳ የከተማ አስተዳደር አመራሮችን ጨምሮ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል

ሚዛን አማን ግንቦት 23/2017 ዓ/ም በሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ተከታታይነት ያለው የጽዳት ዘመቻ በማካሄድ ከተማዋን ውብና ማራኪ ለማድረግ የሚያስችል የጽዳት ዘመቻ ስራ በዛሬው እለት ተጀመረ።

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጅነር ሰለሞን ሌዊ እንደተናገሩት የከተማዋን ፅዳት በዘላቂነት ለመጠበቅ በመንግሰት አቅም ብቻ ሳይሆን የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ንቁ ተሳትፎ እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል

በዚህም የከተማዋ እያንዳንዱ ነዋሪ አካባቢውን በ20 ሜትር ርቀት ፅዳቱን መጠበቅ እንዳለበት አብራርተዋል።

አሁን ላይ በከተማ አስተዳደሩ እየመጣ ያለውን ፈጣን ዕድገትና ለውጥ ይበልጥ ለማስቀጠል የሚያስችል ሰፋፊ የአረንጓዴ ልማት ስራዎች እያከናወነ መሆኑን ከንቲባው ተናግረዋል

በተለይ ባላለፉት ዓመታት የከተማዋን ፅዳት ለመጠበቅና ህብረተሰቡ የፅዳቱ ባለቤት እንዲሆን በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የገለፁት ከንቲባው በቆሻሻ የተደፈኑ ዲች ቦዮችን በመክፈት የማፅዳት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በየሳምንቱ በሚካሄዱ የፅዳት ንቅናቄ ስራዎች ብቻ የአካባቢ ፅዳት አይጠበቅም ያሉት ከንቲባው ማህበረሰቡ ፅዳትን ባህል አድርጎ የአካባቢን ፅዳት ማስጠበቅ ላይ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

አካባቢያችንን ማፅዳት ብቻ ሳይሆን ዳግም የቆሻሻ መጣያ ቦታ እንዳይሆኑ ነዋሪው በባለቤትነት መጠበቅ ይኖርበታልም ብለዋል::

የከተማ አስተዳደሩ ዋና ማዘጋጃ ቤት ኃላፊ ኢንጅነር በረከት ምናሴ በበኩላቸው በከተማዋ የፅዳት፣ የውበት እና አረንጓዴ ልማት ስራዎች በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

በከተማዋ ያለውን የቆሻሻ አወጋገድ ስረአት በተገቢው መልኩ መሆን እንዲችልና ብዙሀኑ ያፀዳውን ጥቂቶች ማቆሸሸ ስለማይገባቸው በህግ ተጠያቂ የማድረጉ ተግባር በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

ከተማን ፅዱና ውብ ለማድረግና ቆሻሻ የአካባቢን ገፅታ እንዳያባላሹ ለነዋሪው ህብረተሰብ በባለቤትነት እንዲጠብቁ የማስተላለፍ ስራዎች እየተሰሩ እንደሆነም አብራርተዋል።

በፅዳት ዘመቻው የተሳተፉ አመራርና የከተማው ነዋሪዎችም ከተማውን ውብና ፅዱ ለኑሮ ምቹ ለማድረግ የተጀመረው ስራ የሚበረታታ መሆኑን ተናግረው ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

በተካሄደው የፅዳት ዘመቻ ላይ የሚዛን አማን ከተማ ከንቲባ ኢንጅነር ሰለሞን ሌዊ፣ የከተማ አስተዳደሩ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊና ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ተስፋዬ ጊስካርን ጨምሮ ሌሎች የከተማ አስተዳደሩ አመራሮችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳታፊዎች ሆነዋል።

ቤንች ሸኮ ዞን ዴንቢ !!!!
31/05/2025

ቤንች ሸኮ ዞን ዴንቢ !!!!

የሚዛን- አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ሌዊን ጨምሮ የዞንና የከተማ አስተዳደር የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ጥራቱን ጠብቆ በመሠራት ላይ የሚገኘውን ምዕራፍ አንድ የሚዛን- አ...
31/05/2025

የሚዛን- አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ሌዊን ጨምሮ የዞንና የከተማ አስተዳደር የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ጥራቱን ጠብቆ በመሠራት ላይ የሚገኘውን ምዕራፍ አንድ የሚዛን- አማን የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴን ጎበኙ።

ሚዛን- አማን ግንቦት 23/2017 ዓ/ም በኮሪደር ልማት ጉብኝቱ ላይ የተገኙት ከንቲባው ኢንጅነር ሰለሞን ሌዊ የኮሊደር ልማት ሥራው ለከተማችን ተጨማሪ ውበትና ለነዋሪዎች ምቹ ብሎም የቱሪስት መዳረሻ ከተማ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን በጉብኝቱ ገልጸዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ውሃ ማዕድንና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ግሩም ተማም በጉብኝቱ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት የኮሪደር ልማት ሥራው ጥራቱን ጠብቆ የክትትል ሥራው በባለቤትነት መንፈስ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።

የከተማ አሥተዳደሩ የብልፅግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የሠንግስት ተጠሪ አቶ ተስፋዬ ጊስካር በበኩላቸው የልማት ሥራው ሌት ከቀን በመንግሥት ላይ እንደሚገኝና በፓርቲ መዋቅሮች ያልተቋረጠ ክትትል እና ድጋፍ ተጠናክሮ እንደ ሚቀጥል ጨምረው ገልፀዋል።

የኮሊደር ልማት ሥራው ከተማችን ምቹና ተመራጭ የስበት ማዕከልነቷን ይበልጥ አጉልቶ እንደ ሚያሳያት በመርሐ-ግብሩ ላይ የተገኙ የመዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጆች በጉብኝታቸው ወቅት አክለው ገልፀዋል።

መሠል የልማት ሥራዎች ከተሞቻችን ይበልጥ ከማዘመን ባሻገር ወጣቱን የሰው ኃይል ክፍል በልማት ሥራው ተሳታፊ በማድረግና የስራ እድል በመፍጠር መንግሥት እየተጋ እንደ ሚገኝ አመራሮቹ በጉብኝት መርሐ-ግብሩ ላይ ገልፀዋል።

ቤንች ሸኮ ዞን "ዴንቢ ሎጅ"!!!!
28/05/2025

ቤንች ሸኮ ዞን "ዴንቢ ሎጅ"!!!!

👉 ❗  ****************  ወጣቱ   የሚዛን አማን ከተማ አስ/ር ማዘጋጃ ቤት ዋና ስ/አስኪያጅ በመሆን ተሹሟል።  ኢንጂነር በረከት በሐዋሳ፣አዳማ እንዲሁም ከሐገር ውጪ በተማረበት መ...
28/05/2025

👉 ❗
****************
ወጣቱ የሚዛን አማን ከተማ አስ/ር ማዘጋጃ ቤት ዋና ስ/አስኪያጅ በመሆን ተሹሟል።
ኢንጂነር በረከት በሐዋሳ፣አዳማ እንዲሁም ከሐገር ውጪ በተማረበት መስክ በማገልገል እምቅ አቅም አካብቷል።በመሆኑም የተወለደበትን አከባቢና ማህበረሰብ ለማገልገል እነሆ ዛሬ ተቀላቅሏል። ከጎኑ በመሆን በማገዝ የክልልና የዞን መናገሻ የሆነችውን ሚዛን አማናችንን አንድ ደረጃ ከፍ እናድርግ!!
ወንድሜ ኢንጂነር በረከት ምናሴ መልካም የስራና የውጤት ዘመን እንዲሆንልህ ከልብ እመኛለሁ::

የክልልና የዞን ከፍተኛ መንግስት አመራሮች በሚዛን አማን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ጎበኙ።በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አ...
24/05/2025

የክልልና የዞን ከፍተኛ መንግስት አመራሮች በሚዛን አማን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ጎበኙ።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማንን ጨምሮ የዞን የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

የመስክ ምልከታው የገበታ ለትውልድ አካል የሆነው የዴንቢ ሎጅ ግምባታና የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ ግምባታ ያለበት ደረጃን ጎብኝተዋል።

በሚዛን አማን ከተማ የዶሮ መንደርና በግል ባለሀብት ተገምብቶ አገልግሎት እየሰጠ ያለውን የሙፍቲ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ተመልክተዋል።

በምልከታው ወቅት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍቅሬ አማን እንደገለፁት ከለውጡ መንግስት ወዲህ በክልሉ ተስፋ ሰጪ ልማቶች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል።
መረጃው የዞኑ መንግስት ኮምኒኬሽን ጽህፈት ቤት ነው።

አከባቢው ከለውጡ በፊት በልማት የተጎዳ በመሆኑ በተደጋጋሚ ህዝቡ ለሚያኘሳቸው ጥያቄዎች የለውጡ መንግስት ደረጃ በደረጃ ምላሾችን እየሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

በሚዛን አማን ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የፌዴራል ፕሮጀክቶች በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙ መሆኑን ገልፀው የዴንቢ ሎጅም ከ95 በመቶ በላይ መድረሱ መመልከት ተችሏል ብለዋል።

የሚዛን አማን አየር ማረፊያ የአስፓልት ስራው የተጀመረ መሆኑን መመልከታቸውን ገልፀው የለውጡ መንግስት ፕሮጀክቶችን ጀምሮ የማጠናቀቅ አቅሙ የተረጋገጠበት መሆኑን ገልፀዋል።

የሚዛን አማን አየር ማረፊያ እዚህ ደረጃ ላይ ለመድረሱ የአከባቢው ማህበረሰብና መንግስት ያደረገው ርብርብ ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።

ኤርፖርቱ ሲጠናቀቅ በአከባቢው ያለው የተለያዩ ሀብቶችን ለማስተዋወቅና አውጥቶ በመሸጥ ለሀገሪቱና ለአከባቢው እድገት ትልቅ አቅም መሆኑን ጠቁመዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን በበኩላቸው በዞኑ እነዚህ ፕሮጀክቶች መገንባታቸው ለማህበረሰቡ ትልቅ መነቃቃትን እየፈጠረ መሆኑን አንስተዋል።

የለውጡ መንግስት የልማት ተጠቃሚነትን ያረጋገጠ መሆኑን ገልፀው የዞኑ ህዝብና መንግስትም እየተከናወኑ ባሉት ፕሮጀክቶች ላይ ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን አንስተዋል።

በሀገራችን ለተመዘገበው ለውጥ የንግዱ ማህበረሰብ ከፍተኛ ሚናን ተጫውተዋል። አቶ ሀብታሙ ካፍትን   "የብልጽግና ጉዟችን እና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ቃል ዞን አቀፍ  የንግዱ ማህ...
23/05/2025

በሀገራችን ለተመዘገበው ለውጥ የንግዱ ማህበረሰብ ከፍተኛ ሚናን ተጫውተዋል። አቶ ሀብታሙ ካፍትን

"የብልጽግና ጉዟችን እና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ቃል ዞን አቀፍ የንግዱ ማህበረሰብ መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

በውይይት መድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን እንደገለፁት የኢትዮጵያ ብልፅግና መረጋገጥ የንግዱ ማህበረሰብ ሚና ከፍተኛ ነው ብለዋል።

ንግድ በኢትዮጵያ ታሪክ ቀደምትና የኢኮኖሚ ማዕከል ሲሆን ፣ ለፈጣንና ቀጣይነት ላለው የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።

የአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ የሀገራችንን የኢኮኖሚ ሽግግር ለማፋጠን የሚያስችሉ በርካታ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ተነድፈው ተግባራዊ እየሆ መሆኑን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

ቤንች ሸኮ ዞን በበርካታ የተፈጥሮ ሀብቶችና ፀጋዎች የተባረከ መሆኑን የገለፁት አስተዳዳሪው ለም መሬት ፣ የተትረፈረፈ ውሃ ፣ የተለያዩ የእንስሳትና የዕፅዋት ዝርያዎች እንዲሁም ማዕድናት በብዛት እንደሚገኙም ተናግረዋል።

በተለይም የቡና ምርት በማስመዝገብ ግንባር ቀደም ሲሆን ፣ የዘይት እህሎች ፣ ፍራፍሬዎች ፣ አትክልቶችና ማር በማምረት ከፍተኛ አቅም አለው ብለዋል። የዞናችን የተፈጥሮ ውበትና የባህል ብዝሃነትም ለቱሪዝም ልማት ትልቅ ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል ሲሉ ገልፀዋል።

በዞኑ የሚገኘኙ ባለሀብቶች በሚዛን አማን ከተማ ለሚገነባው አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ለተነሺዎች ለሚከፈለው የካሳ ክፍያ ያደረጉት አስተዋፅዖ ከፍተኛ በመሆኑ ላደረጉት አስተዋጽኦ አመስግነው ይህ የጋራ ጥረትና አብሮ መስራት የሀገር ግንባታ ዋነኛው ምሰሶ መሆኑንም ገልፀዋል።

የዞኑ የንግድ ማህበረሰብ ይህንን የላቀ ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲያስቀጥል በጋራ ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ንቁ ተሳታፊ በመሆንና ተጠቃሚ በመሆንና የዞናችንንና የሀገራችንን ብልጽግና እንድታረጋግጡ ጥሪዬን አስተላልፈዋል።

ባለሀብቱ በተሰማራበት የንግድ መስክ ሁሉ ምርትና ምርታማነትን መጨመር ፣ ሰፋፊ የስራ ዕድል መፍጠር ፣ በሀገሪቱ በውድድር ላይ የተመሰረተ ፍትሃዊ የግብይት ስርዓት ማስፈን ፣ ህገወጥነትን መከላከል ፣ ለሰላም እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መስፈን እንዲሁም በአለም ገበያ ተወዳዳሪ ሆኖ የሀገር ምርትና አገልግሎትን ለመሸጥ የሚያስችል ሁለንተናዊ አቅም መገንባት ይጠበቅባችኋል ሲሉ ገልፀዋል።

ውይይት ፣ ችግሮችን በግልፅ በመነጋገር ፣ የመፍትሄው አካል በመሆን እና የጋራ አቅማችንን በመጠቀም የብልጽግና ጉዟችንን ለማሳካት ይረዳናል በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በመንግስትና በንግዱ ማህበረሰብ መካከል ያለውን ግንኙነትና መተማመንን ለማጠናከር ይህ መድረክ ትልቅ ሚና ይጫወታል።

ስለሆነም አምራች ኢንዱስትሪያሊስቶች ፣ በልዩ ልዩ ንግድ ዘርፍ የተሰማሩ አካላትና አነስተኛና ጥቃቅን ስራዎች የተሰማሩ የህብረተሰብ ክፍሎች በዚህ ውይይት ላይ በንቃት በመሳተፍ ገንቢ ሃሳቦችን እንዲያቀርቡ አስተዳዳሪው ተናግረወሠል።

ለውይይት መነሻ የሚሆን ሰነድ በቤንች ሸኮ ዞን ንግድና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ በአቶ ኮጁ ባዳካች ቀርቧል።

ባለፉት በለውጥ ዓመታት በተገኙ ስኬቶችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንዲሁም ከንግዱ ማህበረሰብ በሚጠበቀው ሚና ዙሪያ ገለፃ እየተደረገ ሲሆን በቀረበው ሰነድ ላይ ውይይት አየየተደረገ ይገኛል።

በቤንች ሸኮ ዞን የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ በፌደራል መንግስት እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ።"የብልጽግና ጉዟችን እና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና"በሚል መሪ ቃል በዞኑ የሚገኙት የንግዱ ...
23/05/2025

በቤንች ሸኮ ዞን የሚገኙ የንግዱ ማህበረሰብ በፌደራል መንግስት እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ።

"የብልጽግና ጉዟችን እና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና"በሚል መሪ ቃል በዞኑ የሚገኙት የንግዱ ማህበረሰብ በፌደራል መንግስት እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

አልሚ ባለሀብቶቹ ተዘዋውረው ምልከታ ባደረጉበት ወቅት መንግስት በየአካባቢው እኩል የልማት ተጠቃሚነትን እያረጋገጠ እንደሚገኝ መመልከት መቻላቸውን ገልፀዋል።

በዚህም የለውጡ መንግስት የተጀመሩ በርካታ ፕሮጀክቶ የሀገሪቱን ብልፅግና የሚያረጋግጡ በመሆናቸው ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚያስቀጥሉ ተናግረዋል።

ተፈጥሮ ለረጅም ጊዜ ተሸፍኖ ቆይቶ ጠቅላይ ሚኒስተር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በአካል መጥተው ያስጀመሩት የገበታ ለትውልድ አካል የሆነው የዴንቢ ሎጅ ለዞናችን የቱሪዝም ዘርፉን መነቃቃት የፈጠረ ይገኛል ብለዋል።

ይህንን ፕሮጀክት ማየታችን በሌሎች ስራዎች ለእኛም መነቃቃት ፈጥሯል ብለዋል። ዘርፉም ለወጣቶች ስራ በመፍጠርም ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም ተናግረዋል።

የሚዛን አማን ኢንተርናሽናል ኤርፖርት ስራዉ በጥሩ ሆኔታ እየተከናወነ ይገኛል ያሉት ባለሀብቶቹ ስራው ተጠናቆ ላገልግሎት ክፍት ሲሆን ለንግዱ ማህበረሰብ ንግዱን ለማፋጠንና ከሌሎች ከተሞች ጋር ንግዱን ለማስተሳሰር የማይተካ ሚና እንዳለው ገልፀዋል።

የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ የአስፓልት ማንጠፍ ስራ እየተከናወነ ነው።በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሰኔ 13/2013 ዓ.ም የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጦ ስራው የተጀመረው የ...
20/05/2025

የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ የአስፓልት ማንጠፍ ስራ እየተከናወነ ነው።

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሰኔ 13/2013 ዓ.ም የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጦ ስራው የተጀመረው የኤርፖርት ግንባታ የአስፓልት ማንጠፍ ስራ መከናወን ጀምሯል።

ግንባታው ከ78 በመቶ በላይ መድረሱ የተገለፀ ሲሆን በአጭር ግዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑ ተመላክቷል።

አሁን ላይ በርካታ ስራዎች ተጠናቅቀው የአስፓልት ኮንክሪት ግንባታው እየተፋጠነ እንደሚገኝ መመልከት ተችሏል።

 =============================  መቼስ በህይወት እስካለን ድረሰ ሊገጥመን የሚችል ነገር መገመት አዳጋች ነው። ነገሩ እንዲህ ነው ሕፃን ብሌን ሰውአገኝ ተፀንሳ የውልደቷ ጊዜ...
20/05/2025


=============================
መቼስ በህይወት እስካለን ድረሰ ሊገጥመን የሚችል ነገር መገመት አዳጋች ነው። ነገሩ እንዲህ ነው ሕፃን ብሌን ሰውአገኝ ተፀንሳ የውልደቷ ጊዜም ደርሶ በምትወለድበት ወቅት የህክምና ስህተት/technical error ይገጥማትና ከተወለደችም በሗላ እንደማንኛውም ሕፃን መንቀሳቀስና መላወስ በእጅጉ ከባድ ሆነባት።እድሜዋ እየጨመረ በመጣ ቁጥር የውስጥ ፍላጎት ቢኖራትም እንኳን እንደማንኛውም ሕፃን መጫወት መቦረቅ ብርቅ እየሀነባት መጣ የሕፃኗ እንዲህ መሆን ወላጅ አባቷንና እናቷን እረፍት ነሳ። ወደ አዲስ አበባ ፖ/ሆስፒታልም ሪፈር ተደረገች።በአጥንቷ ላይም ጉዳት ስለደረሰባት በየቀኑ ለረዥም ጊዜ በፊዚዮትራፒ እየታየች እንድትቀጥል ዶክተሮች ወሰኑ። በመሆኑም ሙሉ ሕክምናውን በአዲስ አበባ ፖ/ሆስፒታል እየተከታተለች ትገኛለች። ይሁን እንጂ ለአካሏ የሚያስፈልጋት የሕክምና ቁሳቁስና ለተከታታይ ጊዜ ፊዚዮትራፒ የምትከታተልበት የህክምና ወጪ በነፍስ ወከፍ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። ወላጅ ቤተሰቦቿም በየቀኑ ለሚደረግ የሕክምና ወጪ ከአቅማቸው በላየ በመሆኑ ውጪ አማራጭ እንደሌላቸው በመግለፅ በአደባባይ የልጃችንን ነፍስ አድኑልን ሲሉ በፈጣሪ ስም ተማፅነዋል።
ሁሌም የምተማመንባችሁ በሐገርና ከሐገር ውጪ የምትገኙ ሳትሰስቱ የተጨነቀችን ሕይወት ለማትረፍ ለምትረባረቡ ደጋግ እጆች ወገኖቼ ዛሬም እንደወትሮ ነፍስ እንታደግ ስል በፈጣሪ ስም ያቀረብኩትን የድጋፍ ቻሌንጅ እንድትቀላቀሉ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
CBE 1000141137275
መልዕክቱን Like,shareበማድረግ ያጋሩ!!!

በሚዛን አማን ከተማ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ማኅበረሰቡን እያገለገሉ ጥያቄዎቻቸው በህጋዊ መንገድ  እንዲመለሱ እንሰራለን ሲሉ ተናገሩ ከተማ አስተዳደሩ በከተማዋ በሚገኙ በየጤና ተቋማት ያለው...
19/05/2025

በሚዛን አማን ከተማ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ማኅበረሰቡን እያገለገሉ ጥያቄዎቻቸው በህጋዊ መንገድ እንዲመለሱ እንሰራለን ሲሉ ተናገሩ

ከተማ አስተዳደሩ በከተማዋ በሚገኙ በየጤና ተቋማት ያለውን አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የሚያስችል የውይይት መድረክ ከጤና ባለሙያዎች ጋር አካሂዷል፡፡

የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር በከተማዋ ያለውን የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻልና በጤናው ዘርፍ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ያለመ የውይይት መድረክ ከጤና ባለሙያዎች ጋር አድርጓል።

በመድረኩ የተሳተፉ የጤና ባለሙያዎች በየጤና ተቋማት በርካታ ችግሮች ቢኖሩባቸውም እነሱን ተቋቁመው እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የጤና ባለሙያዎቹ ማኅበረሰቡን እያገለገሉ ጥያቄዎቻቸው በህጋዊነት እንዲመለሱ እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።

ባለሙያዎቹ አሁን ላይ ካለው የኑሮ ጫና አንፃር የደመወዝ ጭማሪ፣ የትርፍ ሰዓት ክፍያ እና ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ለኑሮ መሰረታቸው እጅግ አስፈላጊ ቢሆኑም እነዚህ በሕጋዊ መንገድ እንዲፈፀሙላቸው ጠይቀዋል።

የውይይት መድረኩን የመሩት የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ኢንጂነር ሰለሞን ለዊ እንደተናገሩት፤ በከተማዋ የሚገኙ የጤና ተቋማት ለህብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ውይይቱ በከተማዋ በሚገኙ 2 ጤና ጣቢያዎች ላይ የሚሰሩ ባለሙያዎች ለማህበረሰቡ የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉና ያሉባቸውን ችግሮች ለመዳሰስ የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል።

የጤና ባለሙያው የሚያነሳቸው የጥቅማ ጥቅምና የህክምና ግብአቶች ዕጥረት እንዲፈቱ ደረጃ በደረጃ ይሰራል ብለዋል።

በውይይት መድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የከተማ አስተዳደሩ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ጊስካር በበኩላቸው፤ መንግስት ባለፉት የለውጥ አመታት የጤናውን ዘርፍ ለማሻሻልና የህብረተሰቡን እርካታ ይበልጥ ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል ነው ያሉት።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የጤና ባለሙያዎች የተለያዩ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መነሻ በማድረግ የተለያዩ ሀሳቦችን በስፋት እያነሱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በከተማ አስተዳደሩ እነዚህ የባለሙያ ጥያቄዎች በተገቢው እንዲፈቱና በህጋዊ መልኩ ምላሽ እንዲሰጥ ትኩረት ተደርጓል ነው ያሉት።

በዕለቱ የከተማ አስተዳደሩ ጤና ጽ/ቤት ሃላፊ ወይዘሮ ምርታለም ደሳለኝ፤ እንደሀገር በለውጡ አመታት በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ዙሪያ የመወያያ ሰነድ አቅርበው ሰፊ ውይይቶች ተደርገዋል።ደሬቴድ

የቤንች ሸኮ ዞን የመንግሰት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት
ለበለጠ መረጃ ፦

📌 ድረ ገጽ፦ www.benchshekozonecom.gov.et
📌 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/benchshekozonepublicrelationoffice
📌 ዩትዩብ፦ https://youtube.com/?feature=share8
📌 ቴሌግራም፦ https://t.me/bszgca
📌 ትዊተር፦ https://twitter.com/BenchGov?t=V1DGL3YnPHirGEiTq-jh2A&s=09
📌 ሊንክደን :- https://www.linkedin.com/company/benchshekozonegovernmentcommunication/
📌 ኢንስታግራም፦ https://instagram.com/benchshekozonepr?utm_source=qr&igshid=MzNlNGNkZWQ4Mg%3D%3D
📌 ቲክቶክ፦ tiktok.com/
📌 ዋትስአፕ፦ https://whatsapp.com/channel/0029VazwNXAElagqoxvVkP3a
📌 ረዲት :- https://www.reddit.com/u/benchshekozonecom/s/zw3A1v6dPR
በመወዳጀት ይከታተላሉ

የሚዛን አማን አይሮፕላን ማረፊያ ተርሚናል ግንባታ እንዲፋጠን ዞኑ ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን በርካታ ሥራዎች ሰርቷል። ክቡር አቶ ሀብታሙ ካፍትንበቤንች ሸኮ ዞን የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊ...
14/05/2025

የሚዛን አማን አይሮፕላን ማረፊያ ተርሚናል ግንባታ እንዲፋጠን ዞኑ ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን በርካታ ሥራዎች ሰርቷል። ክቡር አቶ ሀብታሙ ካፍትን

በቤንች ሸኮ ዞን የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ላይ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ፣ ግንባታውን ከሚያከናውነው ኮንትራክተር ጋር በግንባታው ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል።

የቤንች ሸኮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀብታሙ ካፍትን እንደገለፁት ዞኑ የአየር ማረፊያ ተርሚናል ግንባታው እንዲፋጠን ከመፈለግ አንፃር ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን በርካታ ሥራዎች መስራቱን ተናግረዋል።

የፌዴራል መንግስት ለካሳ ክፍያ የድጋፍ አማራጮችን የሚያመቻችበት ቢኖር ሲሉም አቶ ሀብታሙ በመድረኩ ላይ አንስተዋል ።

በኮንትራክተሩ ለስራው ሊቀረፉ የሚገባቸውን ተብለው የተነሱ ጉዳዮችን በዞኑ አቅም የሚቀረፉትን ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ዋና አስተዳዳሪው ገልፀዋል።

ኮንትራክተሮች ነፃ የሆኑ ቦታዎች በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቁ ሙሉ አቅም ተጥቀሞ በፍጥነት መስራት ይጠበቃል ሲሉም አቶ ሀብታሙ ጠቁመዋል ።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድሩ የኢኮኖሚና መሰረተ ልማት ጉዳዮች አማካሪ ዶ/ር ምትኩ በድሩ በበኩላቸው በክልሉ እየተሰሩ ካሉ ፕሮጀክቶች ከፍተኛው የሚዛን አማን አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ መሆኑን ጠቁመው ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ወደ አገልግሎት እንዲገባ ከፌደራል መንግስት ጀምሮ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

ከይገባኛል ነፃ ማድረግና ተጨማሪ የተራራዎች ቆረጣ በመኖሩ ከዞኑ ብሎም ከክልሉ አቅም በላይ በመሆኑ የፌደራል መንግስት ድጋፍ አሊያም የረጅም ጊዜ ብድር የሚያመቻችበት ቢኖር ሲሉ ዶ/ር ምትኩ ጠቁመዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ አለማየሁ ይቱስ እንደገለፁት ከልማቱ ቦታ ከ1ሺህ 912 አባወራዎች የተነሱ ሲሆን የዞኑ መንግስት ከ151 ሚሊዮን ብር በላይ ካሳ መክፈሉን ተናግረዋል።

አሁንም ያልተከፈለ 213 ሚሊዮን ብር መኖሩን ጠቁመው ለአየር በረራው ምቹ መሆን ከሳይቱ ውጪ የሚቆረጥ ተራራ ከ52 ሄክታር መሬት በመኖሩ ከዚህም የሚነሱ 590 ሰዎች እና 128 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ አቶ አለማየሁ ጠቁመዋል።

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ኢንጂነር መስፍን ሀይሉ በፕሮጀክቱ ሥራ ላይ በአውሮፕላን ማረፊያው ክልል ውስጥ ያሉ ትንሽ የወሰን ማስከበር ሥራዎች በዞኑ መንግስት ወሰኑ ሊከበር እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ኢንጂነር መስፍን አክለውም ተገማች የሆነ የአየር ፀባይ አለመኖር ሥራውን ከሚያጓትቱ ነገሮች ውስጥ አንዱ መሆኑ ተመላክቷል።

ዞኑ ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን ለአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ እያደረገው ያለውን ሁሉን አቀፍ ድጋፍና አብሮነት ኢንጂነር አመስግነዋል።

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የመጡት በበኩላቸው አውሮፕላን ማረፊያው በተያዘለት ጊዜ መጠናቀቁ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፑን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

በውይይቱና በፕሮጀክቱ ያስተዋሉትን በተደራጀ መልኩ ለተቋማቸው እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል።

የቤንች ሸኮ ዞን የመንግሰት ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት
ለበለጠ መረጃ ፦

📌 ድረ ገጽ፦ www.benchshekozonecom.gov.et
📌 ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/benchshekozonepublicrelationoffice
📌 ዩትዩብ፦ https://youtube.com/?feature=share8
📌 ቴሌግራም፦ https://t.me/bszgca
📌 ትዊተር፦ https://twitter.com/BenchGov?t=V1DGL3YnPHirGEiTq-jh2A&s=09
📌 ሊንክደን :- https://www.linkedin.com/company/benchshekozonegovernmentcommunication/
📌 ኢንስታግራም፦ https://instagram.com/benchshekozonepr?utm_source=qr&igshid=MzNlNGNkZWQ4Mg%3D%3D
📌 ቲክቶክ፦ tiktok.com/
📌 ዋትስአፕ፦ https://whatsapp.com/channel/0029VazwNXAElagqoxvVkP3a
📌 ረዲት :- https://www.reddit.com/u/benchshekozonecom/s/zw3A1v6dPR
በመወዳጀት ይከታተላሉ

Address

Mizan Teferi

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mizan Teferi Official posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Mizan Teferi Official:

Share