06/08/2026
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአርባምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ በነገው ዕለት ይመረቃል
መሶብ በርካታ አገልግሎቶችን በአንድ ማዕከል በመሰብሰብ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፣ ብቃት ያለው ፣ ፈጣንና ከሙስና የፀዳ፣ ዜጎችን የሚመጥን አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ኢንሼቲቭ ነው።
የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚስተዋሉ ቢሮክራሲዎችን በመቀነስ የዜጎችን እርካታ ለማሳደግ ተደራሽ ታስቦ የተጀመረው መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ዜጎች በማዕከሉ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ከቤታቸው ወይም ከሥራ ቦታቸው ሆነው በኮምፒውተርና በሞባይል እንዲያከናውኑ የሚያስችል ነው።
የአርባምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል ውስጥ 4 የፌደራል 5 የክልል ተቋማት በውስጡ የያዘ ሲሆን በአጠቃላይ 32 የተለያዩ የአገልግሎት አይነቶችን ይሰጣል።
በክልሉ ሀለተኛው የሆነው የአርባምንጭ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ፣ የፌደራል እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በነገው ዕለት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል።
የማዕከሉ ግንባታ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን እንዳከናወነውም ተመላክቷል።