Public media entertainment

Public media entertainment ሰላም ለሰዉ ዘር በሙሉ
https://www.youtube.com/

የኔ እናት ተንሰፈሰፍን እኮ😥 አንቺ ሁሌም ኩራት ነሽ 🥺❤
05/09/2026

የኔ እናት ተንሰፈሰፍን እኮ😥 አንቺ ሁሌም ኩራት ነሽ 🥺❤

ሲያምሩ❤
03/09/2026

ሲያምሩ❤

Please ምረጧት
01/09/2026

Please ምረጧት

Please ምረጧት miss 🇪🇹
31/08/2026

Please ምረጧት miss 🇪🇹

በ75ኛው የMiss world በቬትናም በአፍሪካ አህጉር Round ድምፅ1ኛ. ኤርትራ (Snit Habteab TEWOLDEMED...): 5,271,982 ድምጽ2ኛ. ናይጄሪያ (Soye KARIBI-G...
30/08/2026

በ75ኛው የMiss world በቬትናም በአፍሪካ አህጉር Round ድምፅ
1ኛ. ኤርትራ (Snit Habteab TEWOLDEMED...): 5,271,982 ድምጽ
2ኛ. ናይጄሪያ (Soye KARIBI-GEORGE): 2,848,934 ድምጽ
3ኛ. ኢትዮጵያ (Ruth Yirgalem WELDESILA...): 2,298,150 ድምጽ
Come on guys!
ኢትዮጵያውያን በሙሉ ሩት ይርጋለም ወደ ተሻለ ደረጃ እንድታልፍና አገራችንን ወክላ ድል እንድታስመዘግብ ድምፅ በመስጠት እንደግፋት እባካችሁ ሊንኩ ኮሜንት ላይ አለ!

🇪🇹🇪🇹🇪🇹 😘😘💝 🇪🇹🇪🇹

መደበኛ የእርግዝና ክትትል ሳታደርግ ቆይታ ያልተለመደ የጤና ሁኔታ ሲያጋጥማት ወደ ሆስፒታሉ በመምጣት አንዲት እናት አራት ህፃናትን በሰላም ተገላገለችበጎፋ ዞን ሣውላ አጠቃላይ ሆስፒታል አንዲ...
30/08/2026

መደበኛ የእርግዝና ክትትል ሳታደርግ ቆይታ ያልተለመደ የጤና ሁኔታ ሲያጋጥማት ወደ ሆስፒታሉ በመምጣት አንዲት እናት አራት ህፃናትን በሰላም ተገላገለች

በጎፋ ዞን ሣውላ አጠቃላይ ሆስፒታል አንዲት እናት በአንድ ጊዜ አራት ህፃናትን በሰላም መገላገሏ ተገለጸ።እናቲቱና አራቱም ህፃናት በአሁኑ ወቅት በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ከሆስፒታሉ ተገልጿል።

የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስት ዶ/ር ግላንደ ጊሎ እንደገለጹት፣ በሆስፒታሉ ደረጃ ሁለትና ሦስት ህፃናትን በአንድ ጊዜ ማዋለድ የተለመደ ቢሆንም፣ በአንድ ወሊድ አራት ህፃናትን በሰላም ማዋለድ መቻሉ በሆስፒታሉ የመጀመሪያ ጊዜ ነው ብለዋል።

የተቀናጀ ድንገተኛ ቀዶ ሕክምናና የማህፀን ሐኪም ደመቀ ይርጋው በበኩላቸው፣ እናቲቱ በነበረችበት አካባቢ መደበኛ የእርግዝና ክትትል ሳታደርግ ቆይታ፣ ያልተለመደ የጤና ሁኔታ ሲያጋጥማት ወደ ሆስፒታሉ መምጣቷን ገልጸዋል።

በሆስፒታሉ ተገቢው ምርመራ ከተደረገላት በኋላም ለተከታታይ አምስት ቀናት በቅርብ የሕክምና ክትትል ስር ቆይታ፣ አራቱንም ህፃናት በሰላም መገላገሏን ገልጸዋል።

የአራቱ ህፃናት አባት አቶ ናፍቆት ቡሼ፣ ከዚህ ቀደም አምስት ሴት ልጆች እንዳሏቸውና ባለቤታቸው በአሁኑ ወሊድ ደግሞ አራት ሴት ህፃናትን መገላገሏን ተናግረዋል።በዚህም በድምሩ የዘጠኝ ሴት ልጆች አባት መሆናቸውን ገልጸዋል።

ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታዎች በመሆናቸው የተሰጣቸውን በደስታ እንደሚቀበሉ የገለጹት አቶ ናፍቆት፣ ልጆቻቸውን ለማሳደግ ያላቸው አቅም ውስን በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ድጋፍና ትብብር እንዲያደርጉላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

እናቲቱ ወ/ሮ አንድነት አማረ በበኩላቸው፣ ከዚህ ቀደም አምስት ልጆችን መውለዳቸውን ገልጸው፣ በአንድ ጊዜ አራት ህፃናትን መገላገላቸው ለእርሳቸውም ያልተለመደና እንግዳ ክስተት መሆኑን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ መሆናቸውን የገለጹት ወ/ሮ አንድነት፣ ለእርሳቸውና ለህፃናቱ ሕይወት የተረባረቡትን የሆስፒታሉ ሐኪሞችና የጤና ባለሙያዎች አመስግነዋል።

ቤተሰቡ በተለይም አራቱን አዲስ የተወለዱ ህፃናት ጨምሮ ዘጠኙን ልጆች በአግባቡ ለማሳደግ እንዲችል የሚመለከታቸው አካላት ድጋፍና ትብብር እንዲያደርጉለትም ጥሪ ቀርቧል።

Via፦ ጎፋ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን

ለዜድ 😂 ከመልክቱ የዴዚ መጠንከር አስደስቶኛል ፈጣሪ ያፅናሽ ከዚ በላይ ዴዚ ጎበዝ ልጅ
30/08/2026

ለዜድ 😂 ከመልክቱ የዴዚ መጠንከር አስደስቶኛል ፈጣሪ ያፅናሽ ከዚ በላይ ዴዚ ጎበዝ ልጅ

እንኳን ለአባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏ታኅሣሥ 24 ቀን 1212 ዓ.ም ከካህኑ አባታቸው ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኃረያ በእግዚአብሔ...
30/08/2026

እንኳን ለአባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏

ታኅሣሥ 24 ቀን 1212 ዓ.ም ከካህኑ አባታቸው ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ኃረያ በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድና በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ብሥራት ተወለዱ፡፡

ወላጆቻቸውም ፍሥሐ ጽዮን ብለው ሰየሟቸው፡፡ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው መዓርገ ዲቊናን፣ በ22 ዓመታቸው ደግሞ መዓርገ ቅስናን ከግብጻዊው ጳጳስ አባ ቄርሎስ ተቀብለዋል፡፡ በአንድ ወቅት ሕፃኑ ፍሥሐ ጽዮን ወደ ጫካ ለአደን በሔዱበት ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦ ጸጋ መንፈስ ቅዱን አሳደረባቸው፡፡ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወንጌል ወዳልተዳረሰበት ቦታ እንደሚልካቸውም አስረዳቸው፡፡

ቅዱስ ሚካኤልም ከአዳኝነት ሰውን ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ለመመለስ እንደተመረጡ፣ ስማቸውም ተክለ ሃይማኖት እንደሚባል፣ ትርጓሜውም ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት እንደሆነ አበሠራቸው፡፡ ከዚህ በኋላ ያላቸውን ንብረት ዅሉ ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ሰጥተው “አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! የመንግሥተ ሰማያትን በር ትከፍትልኝ ዘንድ እነሆ ቤቴን እንደ ተከፈተ ተውኹልህ” በማለት ቤታቸውን ትተው ወንጌልን ለማስተማር ፈጥነው ወጡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳምም ለ12 ዓመታት ተቀምጠው ከዚያ ሲወርዱ ገመዱ ገመዱ ሲበጠስ ስድስት ክንፍ አውጥተው በረዋል፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምረው በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ተአምራትን በማድረግ በርካታ አሕዛብን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር፤ ከገቢረ ኀጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ መልሰዋል፡፡ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳንጸዋል፡፡

ከዚህ በኋላ በደብረ ሊባኖስ ገዳመ አስቦ ዋሻ በመግባትም በዙሪያቸው ስምንት ጦሮችን ተክለው እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማም፣ ሞትና ነገረ መስቀል በማሰብ በተመስጦ ለ22 ሌሊትና ቀን ያለ ማቋረጥ በጾምና በጸሎት ተወስነው ሲጋደሉ፤ ከመቆም ብዛት የአንድ እግራቸው አገዳ ተሰብራል፡፡ ደቀ መዛሙርቱም የመንፈሳዊ አባታቸውን የዐፅም ስባሪ አክብረው አኑረውታል፡፡ እግራቸው ከተሰበረ በኋላም ለሰባት ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው ሌሊትና ቀን ጸንተው ለሰው ዘር ሁሉ ድኅነትን ሲለምኑ ጥቂት ውኃ እንኳ የቀመሱት በአራተኛው ዓመት ብቻ እንደ ነበረ መጽሐፈ ገድላቸው ይናገራል፡፡ ጻድቁ አባታችን ምድራዊ ሕይወታቸውን በተጋድሎና በሐዋርያዊ አገልግሎት ከፈጸሙ በኋላ ከዚህ ዓለም ድካም የሚያርፉበት ቀን ሲቃረበ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅዱሳን መላእክት፣ ከወዳጆቹ ጋር መጣ፡፡

በስማቸው መታሰቢያ ለሚያደርጉ፣ ለነዳያን ለሚመጸዉቱ ቤተ ክርስቲያን ለሚያሠሩ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸው፣ ስለ ተጋድሏቸው ጽናትም “በሰው እጅ የማይለካውን ይህንን የመንግሥት አዳራሽ ውሰድ” በማለት የጸጋ ልብስ አልብሷቸው፤ በመስቀል ምልክት ያጌጡ ሰባት የሕይወት አክሊላትንም አቀዳጅቷቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም የመንፈስ ልጆቻቸውን ጠርተው ጌታችን የነገራቸውን ዅሉ አስረድተው አባታዊ ምክርና ተግሣፅ ከሰጧቸው በኋላ ነሐሴ 24 ቀን በዘጠና ዘጠኝ ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል፡፡ የመንፈስ ልጆቻቸውም በማኅሌት፣ በዝማሬና በምስጋና ቀብረዋቸዋል፡፡ጌታችንም ነፍሳቸውንም በክብር ተቀብሏታል፡፡ የጻድቁን ቃል ኪዳን ያመኑ ገዳማውያን እንደሳቸው ዓለምን ንቀው በተጋድሎ ይኖራሉ፡፡ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን ከበረከታቸው እንካፈል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

30/08/2026

ጠበቃ ሰበለ ደና ነሽ ሆይ🤗😂

Address

Cabritaberg

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Public media entertainment posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share